የፖለቲካ መፈክሩ፤ “የእኛ ተግባር መማር መማር መማር” የሚለው የሌኒን መርህ ነበር፡፡
አንዲት ልጅ የክፍል ፈተና እያለባት “ፎርፋ” የትም ስትዋልግ ትውላለች፡፡
አባት ይሄንን ጉድ ሰሙና አስጠሩዋት፡-
“አንቺ፤ ለምንድነው ከክፍል የቀረሺው? ሌላው ቀርቶ ትምህርት ቤታችሁ ላይ የተለጠፈውን “የእኛ ተግባር መማር መማር መማር” የሚለውን እንኳን አታስታውሺም?” አሏት፡፡
ልጅቱም፤
“አባዬ፤ ሌኒንኮ ተማሩ አለ እንጂ፤ ተፈተኑ አላለም!” አለቻቸው፡፡