የፖለቲካ መፈክሩ፤ “የእኛ ተግባር መማር መማር መማር” የሚለው የሌኒን መርህ ነበር፡፡
አንዲት ልጅ የክፍል ፈተና እያለባት “ፎርፋ” የትም ስትዋልግ ትውላለች፡፡
አባት ይሄንን ጉድ ሰሙና አስጠሩዋት፡-
“አንቺ፤ ለምንድነው ከክፍል የቀረሺው? ሌላው ቀርቶ ትምህርት ቤታችሁ ላይ የተለጠፈውን “የእኛ ተግባር መማር መማር መማር” የሚለውን እንኳን አታስታውሺም?” አሏት፡፡
ልጅቱም፤
“አባዬ፤ ሌኒንኮ ተማሩ አለ እንጂ፤ ተፈተኑ አላለም!” አለቻቸው፡፡
Published in
ርዕሰ አንቀፅ