አቢሲኒያ የስነጥበብና የሞዴሊንግ ማሰልጠኛ ተቋም ዛሬ ከቀኑ 8 ሰዓት ሁለተኛ የኪነጥበብ ዝግጅቱን እንደሚያቀርብ ገለፀ፡፡ አምስት ኪሎ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተመዘክር ቅፅር ግቢ ውስጥ በሚገኘው የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን አዳራሽ የሚቀርበው ዝግጅት ግጥሞች፣ አጫጭር ጭውውቶች፣ ባህላዊ ውዝዋዜ፣ ዘመናዊ ውዝዋዜን ያካተተ ነው፡፡ የግጥም ምሽትን ከሙዚቃ ጋር ያዋሀደው “ፖዮቲክ ጃዝ” በመጪው ረቡዕ ከምሸቱ 12፡30 በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ይቀርባል፡፡ በዝግጅቱ አርቲስት ግሩም ዘነበ፣ ሜሮን ጌትነት፣ ምስራቅ ተረፈና ሌሎችም ከመለከት የሙዚቃ ቡድን ጋር በመሆነ ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ፡፡