Monday, 07 April 2014 15:29

200 ኢትጵያውያን ስደተኞች ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመሻገር ሲሞክሩ ተያዙ

Written by  አበባየሁ ገበያው
Rate this item
(7 votes)

በህገወጥ መንገድ በኬንያ ድንበር ተሸግረው በታዛንያና፣ በማላዊና በሞዛምቢክ በኩል ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመሻገር ሲሞክሩ በፖሊስ የተያዙት 200 ኢትዮጵያውያን በእስር ላይ ሲሆኑ፤ በርካቶቹም በጉዞ እንግልት በከፍተኛ ህመም ደርሶባቸዋል፡፡
159 ኢትዮጵያውያን የታሰሩት በማላዊ ፓሊስ እንደሆነና የተቀሩት ደግሞ የኬንያን ድንበር ከመሻገራቸው በፊት በኬንያ ፖሊስ እንደተያዙ ታውቋል፡፡
ጫካና በረሃ እየቆራረጡ ወደ ደቡብ አፍሪካ የሚደረገው ጉዞ በውሃ ጥምና በረሃብ በአውሬና በዘራፊ የብዙዎች ህይወት የሚቀጠፉበት በመሆኑ ሴቶች እንደማይደፍሩ የሚታወቅ ሲሆን፤ አሁን የታሰሩት 200 ኢትዮጵያዊያን ወንዶች ናቸው ተብሏል፡፡
ለህገወጥ ደላሎች ከ4ሺህ ብር በላይ በመክፈል በመክፈል ጉዞ ከጀመሩ ስደተኞች መካከል አንዳንዶቹ፣  የያዙት ገንዘብ በዘራፊዎች ተነጥቀው ስንቅም አልቆባቸው ቅጠላ ቅጠልና ሳር ለመመገብ መገደዳቸው ተገልጿል፡፡

Read 2198 times