Monday, 07 April 2014 15:26

የግብፅ ሚ/ር ከባን ኪ ሙን ጋር በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ተወያዩ

Written by 
Rate this item
(8 votes)

   ሰሞኑን በቤልጂየም መዲና ብራሰልስ በተካሄደው የአፍሪካ አውሮፓ ጉባኤ ላይ የተገኙት የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ነቢል ፋሃሚ፤ ከጉባኤው ጎን ለጎን  ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ላይ ጫና ለማሳደር፣ ከመንግስታቱ ድርጅት ዋና ፀሀፊ ባን ኪ ሙንና ከአውሮፓ የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ካትሪን አሽተን ጋር ተወያዩ፡፡
የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፤ በብራሰልስ  የባን ኪ ሙን መኖሪያ ቤት ተገኝተው በታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን ግብፅ በኢትዮጵያ ላይ ጫና ለማሳደር የጀመረችው ዓለም አቀፍ እንቅስቃሴ አካል ነው ተብሏል፡፡ ጉባኤው ከመጀመሩ አንድ ቀን ቀደም ብሎም ሚኒስትሩ ከአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ካትሪን አሽተን ጋር ተመሳሳይ ውይይት ማድረጋቸው ታውቋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ነቢል ፋሂም፤ እዚያው ብራሰልስ ካገኟቸው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሀኖም ጋርም ተወያይተዋል፡፡ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ባለፈው ሰኞ ባወጣው መግለጫ፤“የግብፅን የውሀ ደህንነት ለማስጠበቅ የተቀናጀ የድርጊት መርሀ ግብር ተነድፏል፣ ጉዳዩም ደረጃ በደረጃ እየተሄደበት ይገኛል፣ ይህን የሚያስፈፅም ልዩ የህግ ኮሚቴ ተቋቁሟል፡፡ ግብፅ በአባይ ጉዳይ አዲስ ፋይል አታወጣም፡፡  አባይ የብሔራዊ ደህንነት ጉዳይ ስለሆነ ፖለቲካዊ፣ ህጋዊና  የቴክኒክ ጉዳዮችን ያካተተ መርሀ ግብር ተነድፏል” ብሏል፡፡
በሌላ በኩል በግብፅ የኢትዮጵያ አምባሳደር መሀሙድ ድሪር በአደራዳሪዎች ዙሪያ ሰሞኑን በሰጡት አስተያየት፤ “ግብፅ እና ኢትዮጵያ በግድቡ ዙሪያ ከራሳቸው ውጪ አደራዳሪ አይፈልጉም” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

Read 3457 times