Monday, 31 March 2014 11:42

የወንዝ ምት፣ እንደ ግጥም-ስም

Written by  ገዛኸኝ ፀ- ፀጋው
Rate this item
(5 votes)

ሰው በላቡ ካልገራው፣ ውሀ ብቻውን
ሰው አይፈው-ስም፣
ሀገር በእውቀት ሳይጠመቅ፣ ከድንቁርና
ሰው አይካ-ስም፡፡
‹‹የአባይ ፍቅርም›› ተምሳሌት ነው
መንታ ትርጉም፣ መንታ እውቀት፣
አንድም የሰነፍ ፍቅር ሕይወት፣
አንድም የታላቅ ወንዝ እውነት!
ይህን ቅኔ ያጤነ ሰው፣ ‹‹ነቢይ ባገሩ...››ን
ቢያስታው-ስም፣
የቁጭት ግድቡ ተደርምሶ፣ የሀገር ፍቅሩ
ደለል ቢለብ-ስም፣
እርግጥ ነው አይደፈር-ስም!
እውነት ነው አይደጎ-ስም...
ምስርም አቡን ስትልክ፣ ‹‹ከዕምነት››
አታፋር-ስም፡፡
ለእኛ ጳጳስ ስታበጅ፣ የማጥመቂያ እንኳ
ውሀ አትቀን-ስም¡
በደረቁ የላጨችው ካህን፣ በውሀ ማህሌት
ቢቀስ-ስም፣
የተንኮል ድግምቱ ከሽፏል፤ ዛሬ አባይ ላይ
አይቀድ-ስም፡፡
እናም...ዓባይ
አንተ የወንዝ ምት፣ አንተ የግጥም ስም   
ምስር እውነቱ ቢያንቃትም፣ ያለ እውቀት
የትም አትደር-ስም!
እርግጥ ነው፣ እኛ ሕይወት ከፍለን፣ እርሷ
የነፍስ ውሀ ብታፍ-ስም፣
መጋኛ መሐጸኗን እንደመታው፣ እንዳሶረዳት
ሴት፣ ደም ብታፈ-ስም፣
ከእንግዲህ ዓባይ ድረቅ እንጂ፣ የናስር
ግንቧን አታፈር-ስም!
ሀሩር ምድሯን በውሀ ደፍረህ፣ ድንግል
መሬቷን አትገስ-ስም!
ምስር ‹‹ውል አለኝ›› ብላለች፤ ‹‹በውነት...››
ስልህ ጫፏ አትደር-ስም፡፡
አንተ ሰላማዊ ወንዝ ነህ፤ የተፈጥሮ
ውል አትጥ-ስም!
                  የካቲት 11፣ 2006ዓ.ም

Read 4517 times