Print this page
Monday, 31 March 2014 11:35

“የጠፋው ቤተሰብ” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በየሺወርቅ ወልዴ የተፃፈው እና በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተው “የጠፋው ቤተሰብ” የተሰኘ ልብ ወለድ መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ መፅሀፉ በውስጡ ሌሎች አጫጭር ታሪኮችና ግጥሞች የተካተቱበት ሲሆን ለደራሲዋ ሁለተኛ ስራዋ እንደሆነም ታውቋል፡፡  “የጠፋው ቤተሰብና ሌሎችም” መፅሐፍ 122 ገፆች ያሉት ሲሆን በ35 ብር ለገበያ ቀርቧል። ደራሲዋ ከዚህ ቀደም “አትሮኖስ” የተሰኘ የግጥም መፅሀፍ ለንባብ አብቅታለች፡፡ በሌላ በኩል በገጣሚ ውድነህ ግርማ (የአስቴር ልጅ) የተፃፈው “ሽበቴን ለቅማችሁ” የተሰኘ የግጥም መድበል ሰሞኑን በገበያ ላይ ውሏል፡፡ ከ120 በላይ አጫጭር ግጥሞችን የያዘው መጽሐፉ፤በ65 ገፆች የተቀነበበ  ሲሆን በ30 ብር ይሸጣል፡፡ ግጥሞቹ በፍቅር፣ በማህበራዊ ኑሮ፣ በታሪክና ሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ያጠነጥናሉ፡፡ ወጣቱ ገጣሚ የግጥም መድበሉ የበኩር ስራው እንደሆነ ጠቅሶ ወደፊት ሊያሳትም ያዘጋጃቸው የልብወለድ ስራዎች እንዳሉትም ገልጿል፡፡

Read 2736 times
Administrator

Latest from Administrator