በኢትዮጵያ የቴሌኮም ፕሮጀክቶች ላይ ላለፉት 12 ዓSqƒ ሲሰራ የቆየው ዜድቲኢ፣ አሁን በመካሄድ ላይ በሚገኘው የቴሌኮም ማስፋፊያ ፕሮጀክት 50 በመቶ ድርሻ መውሰዱ የሚታወቅ ሲሆን፤ በኤሌክትሪክ ሃይል ስርጭት፣ በትምህርት አቅርቦትና በከተማ አስተዳደር ዙሪያ ሶስት የቴክኖሎጂ ውጤቶቸን ለኢትዮጲያ ገበያ አስተዋወቀ፡፡
ፓወር ግሪድ፣ ኢለርኒንግ እና ስማርት ሲቲ በመባል የሚታወቁት እነዚህ ቴክኖሎጂዎች የተሣለጠ የከተማ አኗኗር ለመፍጠር የሚያስችሉና በከተማ አስተዳደር ውስጥ ወሳኝ የሚባሉትን መሰረታዊ መረጃዎች በማጠናቀር አመራራርን ዘመናዊ ለማድረግ የሚያግዙ ናቸው፡፡
የኢትዮጲያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት በተገኙበት ለሀገር ውስጥ ገበያ የተዋወቁት የቴክኖሎጂ ውጤቶች በፍጥነት እያደገች ባለችው ቻይና እና በአለም አቀፍ ደረጃ ተተግብረው ከፍተኛ ስኬት ያስመዘገቡ መሆናቸውን ዜድቲኢ ገልፆ፤ በአለም አቀፍ የቴክኖሎጂ አምራችነት ቀዳሚ ስፍራ ለማግኘት አስችለውኛል ብሏል፡፡
ስማርት ሲቲ የተሰኘው ቴክኖሎጂ የ2013 የአለም አቀፍ የሞባይል ቴክኖሎጂ የሽልማት አሸናፊ እንደሆነና በቤጂንግ ከተማ ተተግብሮ የአለም አቀፍን የፈጠራ ተሸላሚ ለመሆን እንደበቃ ኩባንያው ገልጿል፡፡ ኢለርኒግና ፓወር ግሪድ የተባሉት ቴክኖሎጂዎችም ከቻይና በተጨማሪ በሞሪሺየስ፣ ፓፓዋ ኒው ጊኒ፣ በአሜሪካ፣ በቬንዙዌላ እና በኬኒያ ተሞክረው ውጤታማ መሆናቸው ተነግሯል፡፡
በፍጥነት እያደጉ ባሉባት የኢትዮጵያ ከተሞች ውስጥ እነዚህ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ተተግብረው ውጤታማ እንደሚሆኑ ዜድቲኢ ጠቅሶ፤ የኢትዮጵያ የህዝብ ብዛት በ2020 ወደ 120 ሚሊዮን ይደርሳል ተብሎ እንደሚጠበቅና ከዚህም ውስጥ 60 በመቶ ያህሉ በከተማ ይኖራል ተብሎ እንደሚገመት ገልጿል።
Published in
ንግድና ኢኮኖሚ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል