Saturday, 22 March 2014 12:00

ግብፅ አፄ ምኒልክ በተፈራረሙት ውል እየተከራከረች ነው

Written by  ኤልሳቤት እቁባይ
Rate this item
(27 votes)

         ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እየገነባች ያለችው የታላቁ የህዳሴ ግድብ አፄ ምኒልክ በ1902 ከእንግሊዝ ጋር የተፈራረሙትን ውል የሚጥስ ነው ሲል የግብፅ መንግስት ቃል አቀባይ ቢሮ መግለጫ ያወጣ ሲሆን አፄ ምኒልክ ውሉን ሲፈራረሙ የውሀውን ፍሰት አናቆምም እንጂ አንጠቀምበትም በሚል እንዳልተስማሙ ሰነዶች ያመለክታሉ፡፡
 የቃል አቀባይ ቢሮው ባለፈው ረቡዕ ባወጣው መግለጫ፤ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በአባይ ላይ እየገነባች ያለችው ግድብ በ1902 በእንግሊዝ እና በአፄ ምኒልክ የተፈረመውን የሚጥስ ነው፣ አፄ ምኒልክ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ተብለው ስልጣን ላይ ከወጡ በኋላ ከእንግሊዝ ጋር በተፈራረሙት ውል መሰረት ከእንግሊዝ እና ሱዳን ፈቃድ ውጪ  ኢትዮጵያ በአባይ፣ በጣና ሀይቅ እና በሶባት ላይ ምንም አይነት ግንባታ እንደማታደርግ እና ለመንባት የሚሞክሩ ወገኖችንም እንደምትከለክል ተስማምታለች፤
ስለዚህ የአሁኑ ግንባታ ስምምነቱን ይጥሳል ብሏል፡፡ በአለም አቀፍ ህግ የውሀ ባለሙያ የሆኑት አቶ እምሩ ታምራት ጉዳዩን አስመልክተው ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ በመጀመሪያ ደረጃ ግብፅ የ1902 ስምምነት አካል ስላልሆነች፤ ይህን ስምምነት በመከራከሪያ ማንሳት አትትችልም፤ ሌላው የስምምነቱ  የአማርኛ ትርጓሜ  “ኢትዮጵያ ውሃውን ሙሉ በሙሉ የሚደፍን ስራ አትሰራም ይላል እንጂ ጥቅም ላይ አታውል” ብላ አልተስማማችም፡፡

Read 5429 times