Saturday, 15 March 2014 13:11

ማህቶተ ጥበብ ዘልሳነ ግዕዝ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

በመምህርት ኑሀሚን ዋቅጅራ ተፅፎ በኢትጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርቲያን ማህበረ ቅዱሳን አሳታሚነት የተዘጋጀው “ማህቶተ-ጥበብ ዘልሳነ” ግዕዝ መፅሀፍ ለንባብ በቅቷል፡፡ 292 ገፆች ያሉት መፅሐፍ እየጠፋና እየተረሳ የመጣውን የግዕዝ ቋንቋ ለመታደግ ጥረት የተደረገበት ሲሆን በ20 ምዕራፎች ተከፋፍሏል፡፡
መፅሐፉ ስለ ግዕዝ ቋንቋ አመጣጥና ቀዳማዊነት፣ ስለ ግዕዝ ምንነት፣ ስለ ግዕዝ ፊደላትና ስለ በርካታ ጉዳዮች ቅኝት ያደርጋል፡፡ መፅሀፉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን ማህበረ ቅዱሳን ታርሞና ተስተካክሎ የተፈቀደ ሲሆን መታሰቢያነቱ ለፀሀፊዋ የግዕዝ አስተማሪ የቅኔ መምህር እና ጥበብ ፕሮፌሰር መጋቤ ምስጢራት ጌዲዮን መኮንን የተደረገ ሲሆን በ50 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ፀሀፊዋ ከዚህ ቀደም ለአቡነ ጐርጐ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የሚያገለግሉ ከአንደኛ እስከ አራተኛ፣ ከአምስተኛ እስከ ስምንተኛ እንዲሁም ከዘጠነኛ እስከ አስረኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የሚረዱ መፅሀፍቶችን አዘጋጅታለች፡፡
ማህቶተ-ጥበብ ዘልሳነ መፅሀፍ ባለፈው ሳምንት በአማኑኤል ቤተ-ክርስቲያን ተመርቋል፡፡  

Read 4487 times