Print this page
Saturday, 15 February 2014 13:31

ገንዘቤ ዲባባ ለ“ሪኮርድ ሃትሪክ”

Written by 
Rate this item
(4 votes)

ዛሬ በእንግሊዝ በርሚንግሃም በሚካሄደው የ2 ማይል የቤት ውስጥ ውድድር የ23 ዓመቷ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ የውድድር ዘመኑን ሶስተኛ የዓለም ሪከርዷን ልታስመዘግብ እንደምትችል ግምት አገኘች፡፡ ገንዘቤ ባለፈው ሁለት ሳምንት በ3ሺ ሜትር እና በ1500 ሜትር የቤት ውስጥ ውድድሮች ሁለት አስደናቂ የዓለም ሪከርዶችን አስመዝግባለች ዛሬ በበርሚንግሃም “ሳልስበሪ ኢንዶር ግራንድፕሪ” የ2 ማይል ሩጫ  ከ5 ዓመት በፊት በመሰረት ደፋር የተመዘገበውን ክብረወሰን ገንዘቤ ዲባባ ለመስበር እንደምትችል ተዘግቧል፡፡ ከተሳካላት በውድድር ዘመኑ 3 የዓለም ሪከርዶችን ያስመዘገበች ምርጥ አትሌት እንደምትሆን መረጃዎች አውስተዋል፡፡ ገንዘቤ በ2014 የውድድር ዘመን ከገባ ወዲህ በማሳየት ላይ የምትገኘው አስደናቂ ብቃት ከወር በኋላ በፖላንዷ ከተማ ስፖት በሚደረገው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ላይ በ3ሺ እና በ1500 ለድርብ የወርቅ ሜዳልያ ድሎች ግንባር ቀደም እጩም አድርጓታል፡፡
ገንዘቤ ከሳምንት በፊት በስዊድን ስቶክሆልም በ3ሺ ሜትር የቤት ውስጥ ሩጫ  ያሸነፈችው ርቀቱን በ8 ደቂቃ ከ16.60 ሰኮንዶች በሆነ ጊዜ በማጠናቀቅ አዲስ የዓለም ክብረወሰን አስመዝግባ ነበር፡፡ ይህ ሪከርድ አስቀድሞ በመሰረት ደፋር ተመዝግቦ የነበረውን የሰዓት ክብረወሰን በ7 ሰኮንዶች ያሻሻለ ሲሆን ከ1993 እኤአ ወዲህ በ3ሺ ሜትር የቤት ውስጥ ሩጫ ሊመዘገብ ፈጣን ሰዓት ተብሎ ከፍተኛ አድናቆት አግኝቷል፡፡ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ከዚሁ የ3ሺ ማይል አዲስ የዓለም ክብረወሰኗ 5 ቀናት በፊት ደግሞ በጀርመን ካርሉስርህ በተደረገ የ1500ሜትር የቤት ውስጥ ሩጫ በሪከርድ ሰዓት አሸንፋ ነበር፡፡ በ1500 ሜትር የቤት ውስጥ ሩጫው አትሌት ገንዘቤ ያሸነፈችው ርቀቱን በ3 ደቂቃ ከ55፡17 ሰኮንዶች በማገባደድ ሲሆን አስቀድሞ በሩሲያዊ አትሌት ተይዞ የነበረውን ክብረወሰን በ3 ሰኮንዶች አሻሽላዋለች፡፡

Read 2033 times
Administrator

Latest from Administrator