Saturday, 15 February 2014 12:19

የዚንክ ንጥረ ነገርን የያዘው የተቅማጥ ማከሚያ መድሃኒት ጠቀሜታው የጐላ ነው ተባለ

Written by  መታሰቢያ ካሣዬ
Rate this item
(1 Vote)

በህፃናት ላይ እየተከሰተ ለሞት የሚዳርጋቸውን የተቅማጥ በሽታ ለማከም የሚረዳና የZinc ንጥረ ነገርን የያዘው ህይወት አድን ጨው ወይም ኦ.አር.ኤስ እጅግ የጐላ ጠቀሜታ እንዳለውና በተቅማጥ ሣቢያ የሚሞቱ ህፃናትን ቁጥር ከግማሽ በላይ ለመቀነስ እንደሚያስችል ተገለፀ፡፡
DKT ኢትዮጵያ ከትናንት በስቲያ በሐርመኒ ሆቴል ባዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም ላይ እንደተገለፀው ለምለም ፕላስ በሚል ስያሜ እየተዘጋጀ ጥቅም ላይ መዋል የጀመረውና የዚንክ ንጥረ ነገርን የያዘው ህይወት አድን መድሃኒት በተቅማጥ ምክንያት ከህፃኑ ሰውነት ውስጥ የሚወጣውን ፈሳሽ በመተካት ህፃኑ ቶሎ እንዲያገግምና ጉልበት እንዲያገኝ እንዲሁም የምግብ ፍላጐቱ እንዲመለስ ከማድረጉም በላይ ለቀጣዮቹ 2 እና 3 ወራት በተቅማጥ በሽታ እንዳይያዝ ለማድረግ እንደሚያስችልም ተገልጿል፡፡ በተቅማጥ በሽታ የተያዘ ህፃን 10 ፍሬ ዚንክ ከህይወት አድን ንጥረ ነገር (ORS) ጋር መውሰድ እንዳለበትም በዚሁ ጊዜ ተገልጿል፡፡
መድሃኒቱ ከቀጣዩ ወር ጀምሮ በየፋርማሲውና በየጤና ተቋማቱ ውስጥ በስፋት እንዲዳረስ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑም በዚሁ ጊዜ ተገልጿል።  

Read 4715 times