በሲኒማው ዘርፍ አስተዋጽኦ ለማድረግና ለፊልም ተመልካቹ የፊልሞችን ተደራሽነት ለማስፋት እየሠራ እንደሆነ የገለፀው ባታ ሪል እስቴት፤በ22 ማዞሪያ አካባቢ ባስገነባው “ባታ ኮምኘሌክስ” ህንጻ ላይ ዘመናዊ ሲኒማ ቤት እንደሚከፍት አስታወቀ፡፡ በመዲናችን የፊልም ማሣያ ሲኒማ ቤት እጥረት እንዳለ ተገንዝቤያለሁ ያለው ድርጅቱ፤ክፍተቱን ለመሙላት በቅርቡ “አቤል ሲኒማ” ን በመክፈት አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር አስታውቋል።