Monday, 03 February 2014 13:43

በመፃህፍት አከፋፋዮች የዋጋ ተመን ላይ ምክክር ይደረጋል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ደራሲ መስፍን ኃ/ማርያም ይዘከራል “በመፃህፍት የዋጋ ተመንና ዋጋ የመፋቅ ጉዳይ” ላይ ከአከፋፋዮችና አዟሪዎች እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በብሄራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመፃህፍት አዳራሽ ምክክር እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ገለፀ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመፅሃፍ ዋጋ በህትመቱ ላይ ከተገለፀው ውጪ በተለያዩ መንገዶች እየተፋቀና እየተደለዘ በተጋነነ ዋጋ ለአንባቢያን መቅረቡ እንዳሳሰበው የጠቆመው ማህበሩ፤ድርጊቱ ደራሲውንም አንባቢውንም እየጎዳ ነው ብሏል፡፡ የማህበሩ የፅ/ቤት አስተባባሪና የሬዲዮ ፕሮግራም ዋና አዘጋጅ አቶ ደሳለኝ ስዩም ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤በአሁኑ ጊዜ የመፅሃፉ ዋጋ 50 ብር ሆኖ ሳለ 0 በመጨመር 500 ብር እንዲሁም 25 ብር የሚለውን 250 ብር በማድረግ በተጋነነ ዋጋ እየተሸጠ ሲሆን ጉዳዩ በባለድርሻ አካላቱ ትኩረት እንዲያገኝ የዛሬው የምክክር መድረክ ተዘጋጅቷል ተብሏል፡፡ በሌላ በኩል ታዋቂውንና አንጋፋውን የሥነፅሁፍ መምህርና ደራሲ መስፍን ኃ/ማርያም የሚዘክር ዝግጅት በመጪው ማክሰኞ እንደሚካሄድ ማህበሩ አስታወቀ፡፡ “ዝክረ መስፍን ኃ/ማርያም” በሚል የተዘጋጀው ፕሮግራም በብሔራዊ ሙዚየም የሚቀርብ ሲሆን በእለቱ ደራሲው በኢትዮጵያ ሥነፅሁፍ ውስጥ ያበረከተው አስተዋፅኦ እየታሰበ ይመሰገናል ተብሏል፡፡

Read 1862 times