በቶም ፊልም ኘሮዳክሽን የቀረበው “ፅኑ ቃል” ፊልም የካቲት 2 ቀን 2006 ዓ.ም በሁሉም የግል ሲኒማ ቤቶች እንዲሁም
የካቲት 3 በሸራተን አዲስ እና በመንግስት ሲኒማ ቤቶች ለእይታ ይቀርባል፡፡
የ1 ሰዓት ከ50 ደቂቃ ርዝማኔ ያለውን ይህን ፊልም ሠርቶ ለማጠናቀቅ ከአንድ ሚሊዮን ሶስት መቶ ሺህ ብር በላይ ወጪ
የፈጀ ሲሆን ዳንኤል በየነ ዳይሬክት አድርጐት፣ ቶማስ ጌታቸው በደራሲነትና ኘሮዱዩሰርነት ተሣትፎበታል፡፡
የሮማንስ ሰስፔንስ ዘውግ ባለው በዚህ ፊልም ላይ መሪ ተዋናዮቹን እነ ግሩም ኤርሚያስ፣ ማህደር አሰፋና ኤልያስ
ወሰንየለህን ጨምሮ ከ450 በላይ ባለሙያዎች ተሣትፈውበታል፡፡
ቶም ፊልም ኘሮዳክሽን ከአሁን ቀደም “ስርየት” እና “ፔንዱለም” የተባሉ ፊልሞችን በማቅረብ ይታወቃል፡፡
Published in
ዜና