Monday, 27 January 2014 09:15

“ሪፍሌክሽንስ” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

በሮማን ተወልደብርሃን ገ/እግዚአብሄር የተጻፈው “ሪፍሌክሽንስ” የተሰኘ የእንግሊዝኛ ግጥሞችና የፎቶግራፎች ስብስብ መጽሃፍ ባለፈው አርብ በኢትዮጵያ ሆቴል ተመርቆ ለንባብ በቃ፡፡ ነዋሪነቷ በለንደን የሆነው ሮማን፤“የውስጣዊ ስሜቴ ነጸብራቆች ስብስብ ነው” ብላለች- መፅሃፉን።  በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩ 60 ግጥሞችና በመምህር ቶማስ ለማ የተነሱ 26 ፎቶግራፎችን ያካተተው “ሪፍሌክሽንስ”፤ በተለያዩ የመፃህፍት መደብሮችና አዟሪዎች እጅ የሚገኝ ሲሆን በ40 ብር እየተሸጠ ይገኛል፡፡
ገጣሚዋ በቀጣይ የታዋቂ ኢትዮጵያውያን ገጣሚዎችን የተመረጡ ግጥሞች ወደ እንግሊዝኛ በመተርጎም በውጥ አገር ውጭ ተነባቢ ለማድረግና የአገሪቱን ስነጽሁፍ ለተቀረው አለም የማስተዋወቅ ዕቅድ እንዳላት በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ተናግራለች፡፡

Read 2704 times