Print this page
Saturday, 18 January 2014 12:10

ክፍል አራት

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ከባለፈው እትም የቀጠለ
የግል ንግድ ተቋማት ማህበራዊ ሃላፊነትና የህጻናት ጥቅም

ቀደም ባሉት ክፍሎች እንዳየነው የግል ንግድ ተቋማት በማንኛውም የንግድ እንቅስቃሴያቸውና አቅርቦታቸው ውስጥ የህጻናትን ደህንነት የማረጋገጥ ብሎም ምርትና አገልግሎታቸው የህጻናትን ጥቅምና ፍላጎት ያማከለ ስለመሆኑ የማረጋገጥ ሃላፊነት እንዳለባቸው ያስረዳሉ ፡፡ ስድስተኛው መርህ ሽያጭና ማስታወቂያዎች የህጻናትን ደህንነት ማክበርና መደገፍ እንዳለባቸው ያስረዳል፡፡ እንደሚታወቀው ሽያጭና ማስታወቂያ ለማንኛውም ንግድ የደም ስር መሆናቸው ይታወቃል፤ ሆኖም እነዚህ ሁለት እንቅስቃሴዎች ሲካሄዱ በልጆች ላይ ለያደርሱ የሚችሉት ተጽእኖ ብዙም ቦታ ላይሰጠውና ላይተኮርበት ይችላል፡፡ ስለዚህም በማንኛውም መንገድ ምርታቸውን በሚሸጡበት አልያም በሚያስተዋውቁበት ወቅት በህጻናት ላይ ምን ሊያስከትል ይችላል የሚለውን ቅደሚያ ከግምት ማስገባት ያለባቸው ጉዳይ ስለመሆኑ ያስረዳል፡፡

መርሁ የሽያጭ ሂደትም አድልዎ ሊኖርበት እንደማይገባና@ ለተጠቃሚዎች ውሳኔ ይረዳ ዘንድም የምርቶችን ደረጃ በይፋ የማሳወቅ ሃላፊነት እንዳለባቸውም ያስረዳል፡፡ምንም ያህል የጠበቀ ቢሆን፤ የምርት ማስተዋወቅ ሂደትና ማስታወቂያ የአለም አቀፍ የጤና ድርጅትን እንዲሁም ከአገር አቀፍ ደረጃዎች ጋር የሚስማሙ መሆን አንዳለባቸው ያስረዳል፡፡ እንደ መርሁ አገላለጽ የንግድ ድርጅቶቹ በሽያጭ ወይም በማስታወቂያቸው በጎ አመለካከቶችን(አስተሳሰቦችን) ፣ጥቃትን መቃወም እና ጤነኛ የአኗኗር ዘዴን በማንጸባረቅ በተለይም የህጻናት ጥቅሞችን የሚደግፉ መሆን እንዳለባቸው ያስረዳል፡፡

ሰባተኛው መርህ ህጻናት ከአከባቢያቸው፣ ከመሬት ይዞታና አጠቃቀም ጋር ያለቸውን መብቶች ስለማክበርና ስለመደገፍ ይመለከታል፡፡ ህጻናት ከአከባቢያቸው ጋር በተያያዘ ያሏቸው ፍላጎቶች ከግምት ውስጥ ሊገቡ ይገባቸዋል፡፡ አከባቢን አስመልክቶ የሚወጡ ማናቸውም እቅዶችና ሰትራቴጂዎች የህጻናትን፣የቤተሰቦቻቸውን አንዲሁም የማህበረሰቡን ፍላጎት ያማከሉ መሆን እንዳለባቸው ያስረዳል፡፡ በተጨማሪም እነዚሁ እቅዶች በአከባቢና በጤና ላይ ለሚደርሱ ጉዳቶች፣በስራ አጋጣሚ ለሚከሰቱ ጉዳቶች የሚሆኑ የካሳ አከፋፈል ስርአትን የማካተት ሃላፊነት ለነዚህ ተቋማት ይሰጣል፡፡ እንደ መርሁ አገላለጽ በመሬት ይዞታና አጠቃቀም ዙሪያም እነዚህ የንግድ ተቋማት@ ከመኖሪያ ቦታ የመፈናቀል አጋጣሚን በመቀነስና ህብረተሰቡን አሳታፊ በሆነ መልኩ የህጻናትን ጥቅም መከበርን ከግምት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ በተጨማሪም ከአከባቢ ጥበቃ ጋር በተያያዘ የህጻናት የመማር፣የደህንነት፣የጤና፣በቂ ምግብ የማግኘት፣ በጥሩ ሁኔታ የመኖር እንዲሁም የተሳትፎ ፍላጎቶቻቸው ሊከበሩ እነደሚገባም ያስረዳል፡፡ ስለዚህም የንግድ ተቋማት ከአከባቢ እንዲሁም ከመሬት ይዞታ ጋር በተያያዘ የሚያከናውኗቸው ተግባራት@ ለአከባቢ ደህንነት ብሎም ለቀጣዩ ትወልድ አሉታዊ ተጽእኖዎችን ሊያስከትሉ እንደሚችሉ በመገመት ከወዲሁ ለዘላቂ ልማት አስተዋጽኦ ማድረግ እንዳለባቸው ያስረዳል፡፡

Read 1460 times Last modified on Saturday, 18 January 2014 12:25
Administrator

Latest from Administrator