የሥነፅሁፍ ምሁሩን ዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሳን የሚዘክር የኪነጥበብ ዝግጅት ዛሬ ከ3 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት በብሄራዊ ቲያትር ቤት ይቀርባል፡፡ ከ40 ዓመት በላይ በኢትዮጵያ ስነፅሁፍ ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱት ዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ፤ በአሜሪካ ሎስአንጀለስ ዩኒቨርስቲ ውስጥ መምህር ናቸው፡፡ ምሁሩን ለመዘከር በተሰናዳው የኪነጥበብ ዝግጅት፤ የስነፅሁፍ ባለሙያዎች ግጥሞችን፤ ተውኔቶችንና መነባንቦችን እንደሚያቀርቡ የፕሮግራሙ አዘጋጅ አብርሃ ግዛው ኢንተርቴይንመንትና ፕሬስ ሥራዎች ገልጿል፡፡