Saturday, 11 January 2014 12:26

የአርቲስት ፈለቀ ጣሴ የቀብር ሥነሥርዓት በደብረሊባኖስ ተፈፀመ

Written by 
Rate this item
(5 votes)

ለአጭር ጊዜ ታምሞ ባለፈው ረቡዕ በተወለደ በ44 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው አርቲስት ፈለቀ ጣሴ፤ከትላንት በስቲያ በደብረሊባኖስ ገዳም፣ ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈፅሟል፡፡ በአዲስ ከተማ ት/ቤት ለመጀመርያ ጊዜ ከትያትር ጋር የተዋወቀው አርቲስት ፈለቀ፤ በኋላም የአርቲስት ተስፋዬ አበበ ትያትር ክበብን ተቀላቅሏል፡፡ አርቲስቱ በሀገር ፍቅር ትያትር - የጣር ሳቅ፣ የቀለጠው መንደር፣ ጥምዝ፣ የወፍ ጎጆ፣ ባልቻ አባ ነፍሶ እንዲሁም በአዲስ አበባ ትያትርና ባህል አዳራሽ - ቀስተ ደመና፣ የክፉ ቀን ደራሽ፣ የደም ቀለበት፣ ማዶ ለማዶ፣ ፍለጋ፣ ጣይቱ፣ ምርጫው፣ ሶስና እና የታፈኑ ጩኸቶች በተባሉ ትያትሮች ላይ ተውኗል፡፡ ሰርፕራይዝ እና ጥቁር ነጥብ በተሰኙ ፊልሞችም ላይ መስራቱ ይታወቃል፡፡

Read 2467 times