Print this page
Saturday, 11 January 2014 12:24

ጐንደር ዩኒቨርስቲ 60ኛ አመቱን እያከበረ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በ1940ዎቹ የተመሠረተው ጐንደር ዩኒቨርስቲ የተመሰረተበትን የ60ኛ አመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል ለአንድ ዓመት በተለያዩ ዝግጅቶች በማክበር ላይ ይገኛል፡፡ ዩኒቨርስቲው ዘንድሮ ከሚያስመርቃቸው ተማሪዎች በተጨማሪ በዓሉን ምክንያት በማድረግ 3ሺ የቀድሞ ተማሪዎችንም በድጋሚ ያስመርቃል ተብሏል፡፡ ዩኒቨርስቲው በማስገንባት ላይ ያለውን ሆስፒታልም በሰኔ ወር እንደሚያስመርቅ ታውቋል፡፡ በታህሳስ 25 ቀን 2000 ዓ.ም በይፋ የተከፈተው የዩኒቨርስቲው ክብረ በአል የተለያዩ ዝግጅቶች የቀረቡበት ሲሆን ክብረ በአሉ እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ድረስ ይዘልቃል ተብሏል፡፡ ዩኒቨርስቲው ባካሄደው የ6 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድር ላይ ከ2000 በላይ የተሳተፉ ሲሆን የሆቴልና ቱሪዝም ተማሪዎች ለቡርባክስ ህዝቦች መታሰቢያ ያደረጉትን የአዝማሪ ቅኝት አቅርበዋል፡፡ ዩኒቨርስቲው ከመንግስት ጋር በመሆን በማስገንባት ላይ ያለው ባለ አንድ ሺ መኝታ ሪፈራል ሆስፒታል በሰኔ ወር እንደሚመረቅ ተነግሯል፡፡

Read 1420 times
Administrator

Latest from Administrator