Sunday, 05 January 2014 00:00

የአፍሪካ 100 ምርጥ ዩኒቨርሲቲዎች ታወቁ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ53ኛ ደረጃ ይዟል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የአፍሪካ 100 ምርጥ ዩኒቨርሲቲዎች ሰሞኑን ይፋ የተደረጉ ሲሆን የደቡብ አፍሪካዎቹ - ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ሳውዝ አፍሪካ፣ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ኬፕታውንና ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ስቴሌንቦስች ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ያለውን ደረጃ እንደወሰዱ “ፎር አይሲዩ” የተባለው ተቋም አስታወቀ፡፡
የታንዛኒያው ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ዳሬሰላም በአራተኛነት ጣልቃ ቢገባባቸውም፣ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ኩዋዙሉ ናታል እና ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ፕሪቶሪያ አምስተኛና ስድስተኛ ደረጃን  ይዘዋል፡፡ የግብጹ ካይሮ ዩኒቨርሲቲ ሰባተኛ፣ የደቡብ አፍሪካዎቹ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ዊትዋተርስራንድ እና ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ዌስተርን ኬፕ ስምንተኛና ዘጠነኛ ደረጃን ሲይዙ የናይጀሪያው ኦባፌሚ አዎሎሎ ዩኒቨርሲቲ አስረኛ ሆኗል፡፡ የአገራችን አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ  የ53ኛ ደረጃ እንደተሰጠው ለማወቅ ተችሏል፡፡
ግብጽ 20፣ ደቡብ አፍሪካ 19 ዩኒቨርሲቲዎችን በምርጥ መቶዎቹ ውስጥ በማስመረጥ፣ ቀዳሚነቱን የያዙ  ሲሆን  ኬኒያ 6፣ ሱዳን 2 ዩኒቨርስቲዎች ተመርጦላቸዋል፡፡
“ፎር አይሲዩ” የተባለው ተቋም በአህጉራት ደረጃ ምርጥ የሚላቸውን ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች እየመረጠ በየስድስት ወሩ ይፋ ማድረግ የጀመረው እ.ኤ.አ ከ2004 ጀምሮ ነው፡፡ የዓለም ዩኒቨርስቲዎች የፈጠሩትን ተጽዕኖና በድረ ገጾች ላይ ያላቸውን የመረጃ ሽፋን መሰረት በማድረግ የምርጥ ዩኒቨርሲቲዎችን ዝርዝር ይፋ የሚያደርገው ተቋሙ፣ ተዓማኒ፣ ጠቃሚና መልከ ብዙ መረጃዎችን የመስጠት ዓላማ አለው፡፡ የትምህርትና የምርምር ተቋማት  የህትመት ስራዎችንና የምርምር ውጤቶችን በድረ ገጾች እንዲያሰራጩ የበለጠ ተነሳሽነት የመፍጠር ተጨማሪ አላማ እንዳለውም ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 1756 times