Sunday, 05 January 2014 00:00

የአፍሪካ ሞዛይክ የፋሽንና የባህል ትርኢት ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የአፍሪካ ሞዛይክ የፋሽንና የባህል ትርኢት በሚቀጥለው አርብ ምሽት በሸራተን አዲስ የሚካሄድ ሲሆን በዝግጅቱ አለማቀፍ የፋሽን ሞዴሎችና ዲዛይነሮች ይሳተፋሉ፡፡ የአፍሪካን ሞዛይክ ዳይሬክተር አና ጌታነህ እንደገለፀችው፤ አስራ አምስት የውጪና የሀገር ውስጥ ዲዛይነሮች በሚሳተፉበት ትርኢት፤ እውቅ የዘርፉ  ባለሞያዎች ከኒውዮርክ፣ ከደቡብ አፍሪካና ከሴኔጋል ይመጣሉ፡፡ የኢትዮጵያ ምርጥ ሃያ ሞዴሎች የሚሳተፉበት የፋሽን ትርኢት ምሽት የመግቢያ ዋጋ 500 ብር ሲሆን ገቢው ከአዲስ አበባ 55 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው አለልቱ ከተማ ለሚካሄደው የተቀናጀ ልማት ፕሮጀክት ይውላል ተብሏል፡፡ የአፍሪካ ሞዛይክ የፋሽንና የባህል ትርኢት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የአሁኑ ለአስራ አራተኛ ጊዜ መሆኑ ታውቋል፡፡

Read 1725 times