Sunday, 05 January 2014 00:00

“አመፀኛው ክልስ” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(9 votes)

በእናቱ ኢትዮጵያዊ፣ በአባቱ ሆላንዳዊ በሆነው ዳንኤል ጁፕሁክ የተፃፈውና በእውነተኛ ታሪክ ላይ የሚያጠነጥነው “አመፀኛው ክልስ” የተሰኘ መጽሐፍ ሰሞኑን በገበያ ላይ ዋለ፡፡ ደራሲው በ12 ዓመት የእስር ቤት ቆይታው ያሳለፈውን ህይወት ከወህኒ ቤት ከወጣ በኋላ በደች ቋንቋ እንደፃፈው፣ ከዚያም ወደ አማርኛ በመተርጎም እንዳሳተመው ታውቋል፡፡
በአማርኛ ቋንቋ የተተረጐመው መጽሐፍ፤ በአገር ውስጥ በ70 ብር እየተሸጠ ሲሆን በደች ቋንቋ የተዘጋጀው ደግሞ በደቡብ አፍሪካና በአውሮፓ በመሸጥ ላይ እንደሆነ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡

Read 4121 times