በቱሪዝም፣ በወጣቶችና ደም ልገሳ ዙሪያ የሚንቀሳቀሰው “ብራይት ሚሊኒየም ኦሮሚያ”፤ የሦስት ቀናት የሙዚቃ ትርኢትና ባዛር አዘጋጀ፡፡ በአዳማና በሻሸመኔ ከተሞች እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው ማህበሩ፤ ከትርዒቱና ባዛሩ የሚያገኘውን 4ዐ በመቶ ገቢ በከተሞቹ ለሚገኙ የተመረጡ ወጣት ማዕከላትና ትምህርት ቤቶች እንደሚሰጥም ለማወቅ ተችሏል፡፡ በመጪው አርብ የሚከፈተው ዝግጅት በሦስተኛው ቀን እሁድ ይዘጋል፡፡