Print this page
Saturday, 21 December 2013 12:23

ከዓመት በፊት ለተበላሸ ሲሚንቶ ማስቀመጫ ከ30ሺ ብር በላይ ወርሃዊ ኪራይ ይከፈላል

Written by  አበባየሁ ገበያው
Rate this item
(4 votes)

በሶማሌ ክልል በጅግጅጋ ከተማ፣ ለቴሌ ታወሮችና የኔትዎርክ ግንባታ፣ ከጅቡቲ ተገዝቶ የገባው ሲሚንቶ ከአንድ ዓመት በፊት መበላሸቱ ቢታወቅም በወር ከ30ሺ ብር በላይ ለኪራይ እየተከፈለ በግለሰቦች ቤት እንደተቀመጠ ምንጮች ጠቆሙ፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት የጅግጅጋ ቴሌ ቢሮ፤ ለታወሮችና የኔትዎርክ ግንባታ ሁለት ሺ ኩንታል የፓኪስታን ሲሚንቶ ከጅቡቲ ገዝቶ በማስመጣት በግለሰቦች ቤት በየወሩ ከ30ሺ ብር በላይ ኪራይ እየከፈለ ማስቀመጡን የሚናገሩት ምንጮች፤ የዛሬ ዓመት ኮሚቴ ተዋቅሮ ሲሚንቶው ከጥቅም ውጭ እንደሆነ ቢረጋገጥም፣ እስካሁን ድረስ ለኪራይ እየተከፈለ ነው ብለዋል፡፡
የዛሬ ሁለት ዓመት ገደማ የመጋዘን ክፍሉ ሃላፊ በመኪና አደጋ ህይወቱ ማለፉን ተከትሎ መጋዘኑ ተዘግ በመክረሙ ሲሚንቶው ለብልሽት ተዳርጓል ያሉት ምንጮች፤ ለዚህ ተጠያቂው የምስራቅ ጅግጅጋ ሪጅን ቢሮ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡
ይሄም ሳይንስ ቢሮው እነዚህን የተበላሹ ሲሚንቶዎችና ሌሎች ብረታብረቶች ያለምንም አገልግሎት በግለሰቦች ቤት አስቀምጦ፣ በወር ከ30ሺ ብር በላይ ኪራይ በመክፈል መንግስትን ለኪሳራ እየዳረገ መሆኑን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡
በአሁኑ ጊዜም የሪጅኑ ቢሮ፤ ለታወሮችና ኔትዎርክ ግንባታ ከአዲስ አበባ ሲሚንቶ እየገዛ በመጠቀም ላይ እንደሆነ ታውቋል፡፡


Read 1732 times