Saturday, 07 December 2013 12:39

የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ፊልም ፌስቲቫል የዓመቱ ምርጦች

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በሊንኬጅ አርት ሪሶርስ ሴንተር አዘጋጅነት በየዓመቱ የሚካሄደው የፊልም ፌስቲቫልና የፊልም ውድድር ባለፈው ሳምንት

ተካሂዶ አሸናፊዎች ተሸለሙ፡፡
ድርጅቱ ዘንድሮ ለስምንተኛ ጊዜ ባካሄደው ዝግጅት ፊልሞችን በእስር ዘርፎች አወዳድሯል፡፡
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ከኢትዮጵያ ባህልና ቱሪዝምና ከደራሲያን ማህበር የተውጣጡ አምስት የፊልም ባለሞያዎች፣

ፊልሞቹን በተለያዩ ሲኒማ ቤቶች በመመልከት ዳኝተዋል፡፡
ባለፈው ሰኞ በብሔራዊ ቲያትር በተከናወነው የመዝጊያና የሽልማት ስነስርዓት ላይ ይፋ እንደተደረገው “ኒሻን” ፊልም

በሶስት ዘርፎች አሸናፊ ለመሆን በቅቷል - በዓመቱ ምርጥ ፊልም፣ ምርጥ ዳይሬክተርና ምርጥ ሲኒማቶግራፊ፡፡



በወርሃ ታህሣሥ፣ 2001 ዓ.ም ነው … አንዲት ቀይ የቤት መኪና፣ ስድስት ኪሎ ከሚገኘው ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

ዋናው ግቢ፣ በአንደኛ በር በኩል ወጥታ ቁልቁል ወደ አራት ኪሎ አቅጣጫ ከነፈች፡፡ የጣሊያኖችን የግፍ ጭፍጨፋ

ከሚዘክረው ሀውልት ጋ ሥትደርስ፣ ወደ ማርቆሥ ቤተክርሥቲያን ታጠፈችና አሁንም ቁልቁል ወደ አፍንጮ በር

ተተኮሰች፡፡ ሰዓቱ፣ 11፡45 አካባቢ እንደነበረ አሥታውሣለሁ፡፡ ቀዩዋ መኪና፣ የዩኒቨርሲቲው አንድ አንጋፋ መምህር

እያሽከረከሯት ወደ ፒያሳ አመራች፤ የመምህሩን አምስት የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች ብትጭንም፣ ከ12፡30 በፊት፣

አሊያንስ ኢትዮ-ፍራንሴዝ ግቢ የማድረስ ሀላፊነት ተጥሎባታል፡፡ ቀይዋ መኪና ከተቆረጠው ሰዓት በፊት ጥቂት

ደቂቃዎችን ቀድማ ከተባለው ቦታ አደረሠችን፡፡
የአሊያንስ ኢትዮ-ፍራንሴዝ ግቢ፣ ከያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት በወጡ ሙዚቀኞች እንደተቋቋመ በተነገረለት “ሃራ

ሳውንድ ባንድ” አማካኝነት፣ ሞቅ ደመቅ ብሎ ይታያል፡፡ በመሣሪያዎች ብቻ የተቀናበሩ ጣዕመ ዜማዎች ይንቆረቆራሉ፡፡

ውጭ ላይ የተሠናዳው መድረክ፣ በህዝበ አዳም ተሞሽሯል፡፡ አሁን ጨለማው ዐይን ያዝ ከማድረግ አልፏል፤ ትላልቅ

ፓውዛ መብራቶች መድረኩን በብርሃን አድምቀውታል፡፡ የሙዚቃ ቅንብሩ በስፋት መደመጥ ያዘ፡፡ አንድ ገጣሚ መድረኩ

ላይ ወጥቶ በመሣሪያ ቅንብር ከሚወጣው ጣዕመ ዜማ ጋር በወጉ ተለክቶ የተሠፋ የሚመሥል የሰውነት እንቅስቃሴ

ማሣየት ጀመረ፡፡ የውዝዋዜው ሥልት፣ ከሙዚቃው ምት ጋር በእርጋታ እየተዋሀደ ከለብታ ወደ ሞቅታ ሲዛወር፣

የገጣሚው አንደበት ተከፈተ፡፡
ከዚያ ሥልጡን አንደበት ውስጥ የሚወጡ የተመጠኑ የስንኝ ቋጠሮዎች፣ በተለያዩ የሙዚቃ መሣሪያዎች ምጣኔ ዜማ

ታጅበው ሲለቀቁ፣ በታላቅ ኪናዊ የመንፈስ ከፍታ ወደ ሰማየ ሰማያት የሚያርጉ ይመስሉ ነበረ፡፡ እኔ በበኩሌ ግጥም፣

ከዋሽንት ባለፈ በተለያዩ ዘመናዊ የሙዚቃ መሣሪያዎች ቅንብር ታጅቦ ሲቀርብ ሣይ የመጀመሪያዬ ነው፡፡ በመድረኩ ላይ

የተለያዩ ወጣት ገጣሚያን፣ ከሙዚቃው ምት ጋር የስንኞቻቸውን ምት እያዋደዱ በውዝዋዜ ሞሽረው ታዳሚውን

ማስኮምኮም ቀጥለዋል፡፡ መሀከል ላይ ይመስለኛል፣ የቀዩዋ መኪና አሽከርካሪ፣ አንጋፋው የዩኒቨርሲቲ መምህርም

መድረኩን ተቆጣጠሩት፤ ገጣሚው ፕሮፌሰር፣ ከወጣቶቹ ባልተናነሰ፣ እንደውም ካንዳንዶቹ በተሻለ ቆሞ ሲያሥተምር

የዋለ ወገባቸውን ከሙዚቃው ሥልት ጋር አዋደው ማወዛወዝ ጀመሩ፡፡ ግጥማቸውንም ከሙዚቃው ሥልት ጋር እያዋሀዱ

አቀነቀኑት፡፡ ይህ ቀን፣ በኢትዮጵያ የሥነ ጽሁፍ ታሪክ፣ ሥርዓት ባለው መልኩ ግጥም በጃዝ የቀረበበት ዕለት ተብሎ

ሊመዘገብ ይችላል፡፡
የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ እንደማስታውሰው ከሆነ፣ በዕለቱ ግጥሙን በመሣሪያዎቹ ቅንብር ጣዕመ ዜማና በራሡ ሥልታዊ

ውዝዋዜ አጅቦ በማቅረብ መድረኩን የሟሸው ገጣሚ አበባው መላኩ ይመስለኛል፡፡ “ይመስለኛል”ን ያመጣሁት፣

የመጀመሪያው የመድረክ አሟሺ አበባው ነው ወይስ ደምሰው መርሻ? ባለ “አሻራ”ዋ ምሥራቅ ተረፈ ናት ወይስ ሰዓሊዋ

ምህረት ከበደ? ወይስ ደግሞ “ለግጥም ጥም ጠብታ” የበቃው ፍሬዘር አድማሱ? የሚለውን ቀዳሚ ሰው በውል ማስታወስ

ባለመቻሌ ነው፡፡ “እየሄድኩ አልሄድኩም” የሚሉት የቀዩዋ መኪና አሽከርካሪ ዶ/ር ፈቃደ አዘዘ ግን መሀከል ላይ

ማቅረባቸው፣ ብዙ ጥርጣሬ አልፈጠረብኝም። ለማንኛውም ግን፣ ስድስቱ ገጣምያን የዕለቱ ባለ ታሪኮች እንደነበሩ

ለመጠቆም መፈለጌን ብታውቁልኝ አልጠላም፡፡
በርግጥ፣ ግጥም በጃዝ ሥርዓት ባለው ቡድናዊ አደረጃጀት ለመጀመሪያ ጊዜ የቀረበው በ2001 ዓ.ም ነው ቢባልም፣ ለዚህ

የቡድን ዝግጅት ከመብቃቱ በፊት ሌሎች ሙከራዎች እንደነበሩ አንዳንድ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ እስከ አሁን በተገኙ

ማስረጃዎች መሰረት፣ በ2000 ዓ.ም በብሔራዊ ትያትር አበባው መላኩ “ቅናት” የተሠኘ ግጥሙን በሲዲ በቀረበ የሙዚቃ

ቅንብር አጃቢነት ለተመልካች ማቅረቡ ይታወቃል፡፡ በዚህ ዕለት ከታዳሚው ከፍተኛ አድናቆት እንደተቸረው ተነግሯል፡፡

አበባው፣ በብሔራዊ ትያትር መድረክ ግጥሙን ከተቀናበረ ሙዚቃ ጋር ያቀርብ ዘንድ ንቃትና ብርታት የሆነው “ደግ

አይበረክትም” የተሠኘው የግጥም ሲዲው ዝግጅት ሊሆን እንደሚችል እገምታለሁ፡፡
እንግዲህ፣ ግጥምን በጃዝ መድረክ የሚያቀርበው የቡድን አባላት በአሊያንሥ ኢትዮ-ፍራንሴዝ ዝግጅትና በኋላም

በተለያዩ መድረኮች ግጥም በጃዝ ማቅረቡን እየሠለጠነበት መጣ፡፡ ቡድኑ፣ ከታዋቂው የፒያኖ ተጫዋች ግርማ ይፍራሸዋ

ጋር በጣሊያን የባህል ማዕከል ያቀረበው ዝግጅት፣ የወደፊቱን የከፍታ ዘመን አመላካች ነበረ ማለት ይቻላል፡፡ በቦሌ

ሮክና በሸራተን አዲስ መድረኮች ላይም ኢትዮጵያዊ ግጥም በጃዝ ተሞሽሮ ይቀርብ ዘንድ የቡድኑ የላቀ ትጋትና ጥረት

ቀጠለ፡፡ በ2003 ዓ.ም፣ ወር በገባ የመጀመሪያው እሮብ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል መድረክ ላይ ከመለከት ባንድ ጋር በኋላም

ከአቢሲኒያ ባንድ ጋር በመተባበር ግጥም በጃዝ እየሸመኑ ማቅረብ ተወዳጅ ኪነት እየሆነ መጣ። የዋቢ ሸበሌው የአንድ

ዓመት የግጥም በጃዝ ጉዞ ሲስተናበር የነበረው በቸርነት ወልደ ገብርኤል፣ በደምሰው መርሻና በአበባው መላኩ እንደነበረ

ያሠባሠብኳቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በዚሁ ዓመት ወደ ኋላ ላይ ግሩም ዘነበና ሜሮን ጌትነት የቡድን አባላቱን

እንደተቀላቀሉ ሰምቻለሁ፡፡
አሁንም የግጥም በጃዝ መድረኮች፤ የታዳሚን ቀልብ እየገዙ፣ የኪነት ልክፍት ያለበትን እያፈዘዙ፣ የገነገኑ ሀገራዊ

ሰንከፎችን እየመዘዙ የስኬት ጉዟቸውን ተያያዙት፡፡ በ2004 ዓ.ም፣ ግጥም በጃዝ በራስ ሆቴል መድረኮች ላይ አብቦ

ይፈካ ዘንድ ጊዜው ፈቀደ፡፡ ወር በገባ የመጀመሪያው እሮብ የራስ ሆቴል ትልቁ አዳራሽ፣ በታዳሚዎች መጣበብ ጀመረ።

የሆቴሉ ሰፊ ግቢ ሊሸከመውና ሊያስተናግደው ከሚችለው በላይ በሆኑ ረዣዥም ሰልፎች ይፈተን ዘንድ ግድ አለው፡፡

አዳራሹ፣ ከ800 በላይ የሚሆኑ ታዳሚዎች ጢም ብለው ሞልተው ይፈሡበታል፡፡ የሚገርመው ግን ይህ ሁሉ ታዳሚ

የሚርመሰመሰው ዝግጅቱ የሚቀርበው በነፃ ሥለሆነ እንዳይመሥልዎ! 50 ብር የመግቢያ ዋጋ ለመክፈል የተሠለፉ

የግጥም በጃዝ እድምተኞች፣ አዳራሹ እየሞላባቸው ሲመለሱ ማየት የየዕለቱ ክሥተት ሆኗል፡፡
የራስ ሆቴሉ ግጥምን በጃዝ መድረክ አሠናጂ የቡድን አባላት፣ ለግዜው “ጦቢያ ግጥም በጃዝ” በሚል ሥያሜ፣ ድርጅት

ከፍቶ የኢትዮጵያን ግጥም በጃዝ አፍክቶ ማቅረቡን ተያይዞታል፡፡ በራስ ሆቴል መድረክ ወር በገባ በመጀመሪያው ዕለተ

እሮብ፣ ለጥበብ ሱሰኞች ምሣቸውን እያደረሠ ይገኛል። የቡድኑ የጥበብ ጉዞ ሥርዓት ባለው መንገድ እየተጓዘ፣

ለተከታታይ 28 ወሮች በመድረክ ላይ ነግሷል፡፡ ቡድኑ፣ ዝግጅቱን በተከታታይ ማቅረብ የጀመረበትን ሁለተኛ ዓመትም

ለማክበር በቅቷል፤ በዚሁ በዓል ላይ፣ የተመረጡ ዝግጅቶች፣ “ጦቢያ ግጥም በጃዝ” (ቅጽ አንድ) በሚል ስያሜ በዲቪዲ

አሣትሞ በ50 ብር ዋጋ ለጥበብ ወዳጆች ማቅረቡ ይታወቃል፡፡ በነገራችን ላይ በራስ ሆቴል መድረክ በጃዝ የሙዚቃ

ቅንብር ተከሽነው የሚቀርቡት ግጥሞች ብቻ አይደሉም፤ ስሜት ኮርኳሪ፣ መሣጭና እውቀት አጋሪ የሆኑ ወጐችና

ዲስኩሮችም ሢቀርቡ አይቻለሁ፡፡ እንደውም፣ በጦቢያ ግጥምን በጃዝ ቢሮ ውስጥ በተገኘ መርሐ ግብር መሠረት፣

በየዕለት መድረኩ 5 ገጣምያን፣ 1 ወግ ተራኪ እና1 ዲስኩር አቅራቢ የኪነት ቤተኞች ሥራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ

ይታወቃል፡፡
የዛሬ የጦቢያ ግጥም በጃዝ ቡድን ተጠሪዎች፤ አበባው መላኩ፣ ምሥራቅ ተፈራ፣ ደምሰው መርሻ፣ ምህረት ከበደ፣ ግሩም

ዘነበና ሜሮን ጌትነት ሲሆኑ፣ አብዛኞቹ፣ በዘመነኛ ትንታግ ገጣሚነታቸው ይታወቃሉ፤ በመካከላቸው በትወናም

የተጨበጨበላቸው ይገኛሉ፡፡ ከ1990ዎቹ መጀመሪያ ጀምሮ አብዛኞቹ የቡድን አባላት በተለያዩ መድረኮች በግጥም

ተናግረዋል፤ ለግጥም ተዋድቀዋል፤ ስለ ግጥም አንብተዋል፤ ስለ ግጥም ቆመዋል፤ ለግጥም ጦም አድረዋል፡፡ ዛሬ ግን

በግጥም እያሠቡ፣ በግጥም ትውልድ ይሞግታሉ፤ በግጥም ተከብረው፣ በግጥም በልተው አድረዋል፡፡
ዛሬ ይህ ቡድን፣ ከተለያዩ ኤምባሲዎችና ከተለያዩ ድርጅቶች የአብረን እንስራ ጥሪ ይቀርብለታል። በታወቁ ተቋማት

ስፖንሰርነት፣ የተለያዩ ሀገራዊ ጉዳዮችን ይወጣ ይዟል፡፡ ለምሣሌ በመጋቢት ወር 2005 ዓ.ም፣ ከያኒው ሰርክ

የሚጠበብበት ተፈጥሮ፣ ህልውናዋ አደጋ ላይ መውደቁን ለማጠየቅ፣ በብሔራዊ ትያትር መድረክ “ጥበብ ለተፈጥሮ”

በሚል ርዕስ የተደነቀ ዝግጅት አቅርቧል፤ በዕለቱ የቀረቡት ግጥሞች በ80 የፖሊስ የማርሽ ባንድ አባላት ታጅበው

እንደነበረ ይታወሣል፡፡
ዛሬ፣ “ጦቢያ ግጥም በጃዝ” የቡድን አባላት፣ የራስ ሆቴልን መድረክ በጥበብ አድምቀው የሚሞሸሩት፣ በራሣቸው

“የመንፈስ ከፍታ” ያህል ብቻ በመንጠቅ አይደለም፤ የተለያዩ ገጣሚዎችን፣ ወግ አራቂዎችን፣ ዲስኩር አቅራቢዎችን ወዘተ

በመጋበዝ አዳዲስ ጥበበ ቃላት እንዲከሸኑ ሥርዓት ዘርግተዋል እንጂ፡፡ ለዚህ ነው፣ ከእግረ ተከል የኪነት ባለሟሎች

እስከ ጉምቱ የጥበብ አያቶች ድረስ በመድረክ ላይ ሢዘምኑ የሚታየው፤ በእውነትና በእውቀት እየተመሙ፣ ኪናዊ ውበት

ሲያፈልቁ የሚገኘው፡፡
ዛሬ ግጥም በጃዝ መድረክ የሚደነቅና የሚወደድ ውበት ብቻ ሣይሆን የሚናፈቅ ሕይወትም እየሆነ ያለ ይመሥላል፡፡

ዛሬ፣ 50 ብር ከፍለው የሚታደሙ አድናቂዎች ብቻ አይደለም የሞሉት፤ የዓመታት ወጪ ሸፍነው የቡድኑ አባል ለመሆኑ

የሚታትሩ ጭምር ተመዝግበዋል እንጂ፡፡ ዛሬ ቡድኑ፣ ጥበብን የሚያቀርብበት የነፃ አዳራሽ መንግሥት ይፍቀድልኝ

አይልም፤ እንደውም በየወሩ ለመንግሥት በሺዎች የሚቆጠር ብር ይገብራል እንጂ፤ “ግብር አይደለም ዕዳ” እንዲል

የገቢዎች ሚኒስቴር፡፡
ምን አለፋዎት … ግጥም በጃዝ መድረክ ላይ በሃበሻ ግጥም፣ የሀበሻ እውነትና እውቀት በጥበባዊ ሥልት ተፈታትቶ

በምርጥ የቃላት ጡብ፣ ሢገጣጠም ያያሉ (እመኑኝ እያጋነንኩ አይደለም-በፍፁም)፡፡ ከሃበሻ የኑሮ ልማድ ውስጥ

እውነቱና እውቀቱ በብልሃት ይተነተናሉ-በግጥም፡፡ ከእውነቱና ከእውቀቱ የተጠነፈፈው ማንነቱ በቃላት ምታት መድረክ

ላይ ሢሠጣ፣ ታዳሚው እየሣቀ ይተክዛል፤ እያጨበጨበ ይቆዝማል፡፡ ግጥሞቹ፣ ወጉና ዲስኩሩ በሀበሻ የመንፈስ ክር

የተሣሠሩ ሽንፈቶቹን፣ ቁጭቶቹን፣ ህልሞቹን ይናገራሉ፤ ከሀገር እውቀቶቹና እውነቶቹ ጋር እየተጣቀሡም፣ የዘመን

መንፈስን እያሥጠቀሡ፣ ገዝፈውና በዝተው ይቀነቀናሉ፡፡ የአዳሚም የታዳሚም መንፈስ ከፍ ብሎ ይንሣፈፋል፤ ዝቅ

ብሎም ይነፍሣል … እኔ በበኩሌ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በመምህርነትም በተማሪነትም ያጣሁትን የመንፈሥ ልዕልና በዚያ

አዳራሽ ውስጥ የተጐናፀፍኩ አይነት ነው የሚሠማኝ፡፡ የሀበሻ ግጥም፣ ወግና ዲስኩር በተቀናበረ ሙዚቃ ታጅበው

እውነት፣ እውቀትና ውበት በሚያፈልቁበት በዚህ አዳራሽ፣ የሰዓታት ሰላም ያገኘሁ ይመሥለኛል፡፡
እስኪ በራሥ ሆቴል አዳራሸ ከሚቀርቡ ዝግጅቶች መካከል የቅርቡን (ህዳር 4 ቀን 2006 ዓ.ም) የጥበብ ድግሥ

በጨረፍታ ልጠቁማችሁ። እንደተለመደው ትልቁ አዳራሽ ከአፍ እስከ ገደፉ ጢም ብሏል፡፡ የውጭ ሀገር የመገናኛ

ብዙኃን ባልደረቦች ትላልቅ መቅረፀ ምሥል ካሜራዎችን ተሸክመው ዝግጅቱን ለመቅረጽ ከወዲያ ወዲህ ሽር ጉድ

ይላሉ፡፡ “ነፃ አውጪ ባንድ” በመሣሪያ የተቀነባበሩ ጣዕመ ዜማዎችን ያሠማሉ፡፡ የመድረክ አጋፋሪው፣ ዝነኛው ተዋናይ

ግሩም ዘነበ ወደ መድረኩ ጐራ እያለ በአስገምጋሚ ድምፁ መርሐግብሩን ያሥተዋውቃል፡፡
በዚህ ዕለት፣ የሸገር ሬዲዮ ባልደረባው ስመ ጥሩ የመድረክ ሰው ተፈሪ ዓለሙ፣ የሁለት ትውልዶችን ብጭቅጫቂ ኑሮ በ

“ስውር-ስፌት” እየጠቀመ ያለው (“ጠ” ጠብቃ ትነበብ) የአዲስ አድማሱ ዋና አዘጋጅ ገጣሚ ነቢይ መኮንን፣ ሢያሻው

በግጥም መናገር የሚችለው ታዋቂው ሰዓሊና ቀራፂ በቀለ መኮንን፣ የዕለቱን መድረክ “የመንፈስ ከፍታ” አግዝፎ የናኘው

ገጣሚ በረከት በላይነህ፣ ለግጥም ወይም ስለ ግጥም ሕይወተን እየከፈለ ያለ የሚመሥለኝ ገጣሚ ደምሰው መርሻ፣ መሪር

ሰዋዊ ግዙፍ ጥያቄዎች በተራኪ ግጥም እንዴት በብልሃት ሊቀርብ እንደሚችል በገቢር ያሣየው ገጣሚ ፈቃዱ ጌታቸው፣

ይህ ትውልድ ከሃገሩ አልፎ ዓለምን የመሞገት ብቃት እንዳለው በአንድ የወግ ጽሁፉ ማሣመን የቻለው የ“ፋክት”

መጽሔቱ አምደኛ ሚካኤል ዲኖ እና በተለያዩ መድረኮች ዝናን ያተረፉት የ“ፋቡላ ኪነጥበብ” አባላት የራስ ሆቴልን

አዳራሽ በሀበሻ የጥበብ አየር ሞልተውት አምሽተዋል፡፡ የታዳሚውን ስሜትና የመንፈሥ እርካታ እንዲህ ነው ማለት

ይከብደኛል፤ የአጋነንኩ ይመስልብኛልና! እራስዎት ጠይቀው ቢያረጋግጡ ይሻላል፡፡ አዘጋጆቹ፣ የ“ጦቢያ ግጥም በጃዝ”

ቡድን አባላት ብራቮ!

Read 2275 times