Saturday, 30 November 2013 11:26

የቻይና ኩባንያዎች የ30 ቢ.ብር የቴሌኮም ማስፋፊያ ስራ ጀመሩ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

   ህዋዌ እና ዜድቲኢ ከተሰኙት የቻይና ኩባንያዎች፣ ለሁለት አመታት ድርድር የተካሄደበትን የ30 ቢሊዮን ብር ማስፋፊያ ፕሮጀክት እኩል ተካፍለው ሰሞኑን ሥራ እንደተጀመሩ የገለፀው ኢትዮ ቴሌኮም፣ በሁዋዌ የሚከናወነው የአዲስ አበባ ማስፋፊያ ፕሮጀክት በስምንት ወራት እንደሚጠናቀቅ አስታወቀ፡፡
ኦፊሰሩ ሐሙስ ከሰዓት በኋላ በኢትዮ ቴሌኮም ዋና መስሪያ ቤት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት አጠቃላይ የማስፋፊያ ስራው በሚሰራበት ወቅት የኔት ወርክ መቆራረጥ ሊያጋጥም እንደሚችልና ህዝቡ ይህን ሊያውቅ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
1.6 ቢሊዮን ዶላር (30 ቢሊዮን ብር ገደማ የተመደበበት) የማስፋፊያ ስራ 50 በመቶው በህዋዌ ቀሪው 50 በመቶ ደግሞ በዜድቲኢ እንደሚሰራ የገለፁት ኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ኦፊሰር አቶ አብዱራሂም አህመድ፣ ሁለቱም ኩባንያዎች እያንዳንዳቸው 18 ሚሊዮን የሞባይል መስመሮችን የሚያስተናግድ የማስፋፊያ ስራ እንደሚያከናውኑ ተናግረዋል፡፡ የማስፋፊያው ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ፣ ኢትዮ ቴሌኮም 59 ሚሊዮን የሞባይል መስመሮችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል ብለዋል -አቶ አብዱራሂም ድርድሩ ሁለት አመት የፈጀበትን ምክንያት የተጠየቁት አቶ አብዱራሂም፣ ፕሮጀክቱ እጅግ ትልቅ ከመሆኑም በላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ያስፈልገዋል ብለዋል፡፡
የኔትወርክ መቆራረጥ መባባሱን በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄም፣ በአገሪቱ ያሉ አራት ሺህ ገደማ አንቴናዎች በመብራት እንደሚሰሩና መብራት ሲጠፋ የኔትወርክ መቆራረጥ እንደሚያጋጥም ተናግረዋል - አቶ አብዱራሂም፡፡
የኦፕቲክ ፋይበር መስመር ላይ የተበራከተው የመቆረጥ አደጋም ትልቅ እክል ሆኗል ያሉት አቶ አብዱራሂም፣ የመቆረጥ አደጋ ይደርሳል” ብለዋል፡፡ ከማስፋፊያ ፕሮጀክቱ በተያያዘም፣ ስራው እስኪጠናቀቅ ድረስ የኔትዎርክ መቆራረጥ እንደሚያጋጥም አቶ አብዱራሂም ተናግረዋል፡፡

Read 2185 times