Sunday, 24 November 2013 17:20

የአንዷለም አራጌ “ያልተሄደበት መንገድ” መፅሀፍ ነገ ይመረቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(9 votes)

የሽብርተኝነት ክስ ቀርቦበት የእድሜ ልክ እስራት የተፈረደበት የአንድነት ፓርቲ አመራር አንዷለም አራጌ፤ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ውስጥ የፃፈው “ያልተሄደበት መንገድ” የተሰኘ መጽሐፍ መታተሙ የሚታወቅ ሲሆን፤ ነገ በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት እንደሚመረቅ ፓርቲው አስታወቀ፡፡
የአንዷለም አራጌ ባለቤትን ጨምሮ የፖለቲካ እስረኛ ቤተሰቦች በምረቃው ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል ያሉት የፓርቲው ተወካይ አቶ ዳንኤል ተፈራ፤ በመጽሐፉ ላይ ከአቶ አስራት አብርሃም ትንታኔ በተጨማሪ ታዋቂ ግለሰቦች የውይይት ሃሳብ እንደሚያቀርቡ ገልፀዋል፡፡
“ምረቃውን የምናዘጋጀው፤ አንዷለም በእስር ቤት ሆኖ ይህን የመሰለ መጽሐፍ በመፃፉ ለማበረታታትና አጋርነታችንን ለመግለጽ ነው” ያሉት አቶ ዳንኤል፤ የአስር ቤቱን ችግሮችና የእስረኛ ስለላን ተቋቁሞ መጽሐፉን ለህትመት ማብቃቱ ያስደንቃል ብለዋል፡፡          

Read 2353 times