ደረጄ መኮንን ከ”አይቤክስ” የሙዚቃ ቡድን ሌላ ከ”ሸበሌ”፣ ከ”ዘመኮንንንስ”፣ “ጊዜ”፣ እና ሌሎች ቡድኖች ጋር አብሮ የሰራ ሲሆን በ1977 ዓ.ም ሺካጎ ላይ የተመሠረተው የ”ዳሎል” የሙዚቃ ቡድን መስራች አባል ነው፡፡ ደረጄ ካቀናበራቸውና የሙዚቃ መሳርያ ከተጫወተባቸው ታዋቂ ዘፈኖች መካከል የኤፍሬም ታምሩ የመጀመርያ አልበም “ጀማዬ”፣ የአስቴር አወቀ “ሰኞ እለት”፣ የእጅጋየሁ ሽባባው “አቦ ሸማኔ” እንዲሁም ከጥላሁን ገሠሠ፣ ማህሙድ አህመድና ከቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ጋ “መሀረቤ” የተሰኘ አዲስ ሥራ ሰርቶ ማጠናቀቁም ተገልጿል፡፡