Print this page
Saturday, 26 October 2013 13:17

የግሪክ ኮሙኒቲ ት/ቤት የተባበሩት መንግስታት ቀን አከበረ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በአዲስ አበባ በሚገኘው የግሪክ ኮሙኒቲ ስኩል የሚመሩ ህፃናትና ታዳጊዎች ከአንድ ወንዝ የተቀዱ አይደሉም፡፡
ከ60 በላይ የተለያየ ዜግነት ያላቸው በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችን የሚያስተናግድ ት/ቤት ነው። የ60 አገራት ተወላጅ የሆኑ ተማሪዎች ስላሉበትም ነው፤ የተባበሩት መንግስታት ቀን በየአመቱ በትምርት ቤቱ የሚከበረው፡፡ ትናንት አርብ ረፋዱ ላይ በተከናወነው ክብረ በዓል፣ የባንዲራዎች ሰልፍ የተካሄደ ሲሆን፤ የግሪክ፣ የምዕራብ አፍሪካ፣ የህንድ እና የኢትዮጵያ የዳንስ ወይም የውዝዋዜ ትርዒት በተማሪዎች ቀርቧል፡፡
በክብረ በዓሉ ላይ የተባበሩት መንግስታት ተወካዮችና የመንግስት ባለስልጣናት በእንግድነት መገኘታቸውን አስተባባሪው ጆሴፍ ፍራንሲስ ገልፀዋል፡፡

Read 1247 times
Administrator

Latest from Administrator