ሪም የህፃናት ሞግዚት ማሰልጠኛ ተቋም፣ ለሶስት ወራት ያሰለጠናቸውን 200 ተማሪዎች ዛሬ በሆሊሲቲ ሲኒማ አዳራሽ ያስመርቃል፡፡
ከአዲስ አበባ የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ እውቅና ያገኘው “ሪም”፣ እውቅና ያለው በየሶስት ወሩ 200 ያህል ሞግዚቶችን ከማሰልጠንም በተጨማሪ ስራ እንደሚያስቀጥር ተገልጿል፡፡
ስልጠናው የህፃናት አስተዳደግን፣ የህፃናት የተመጣጠነ ምግብ ዝግጅትን፣ የህፃናት ጨዋታ አመራረጥ ፣ የመጀመሪያ ደረጃ የህክምና እርዳታ አሰጣጥን ያካትታል ተብሏል፡፡
Published in
ዜና