Saturday, 19 October 2013 10:56

ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ የ“ሲ ኤን ኤን መልቲ ቾይዝ” ተሸላሚ ሆነ

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(1 Vote)

በሽብር ወንጀል የ14 ዓመት እስር ተፈርዶበት በማረሚያ ቤት የሚገኘው የቀድሞው የ“አውራምባ ታይምስ” ጋዜጣ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ባደረገው ሲኤንኤን “መልቲ ቾይዝ” የሽልማት ድርጅት ተሸለመ፡፡
ጋዜጠኛው ሽልማቱን ያሸነፈው በአፍሪካ የነፃ ፕሬስ ዘርፍ ሲሆን ደቡብ አፍሪካ በተካሄደው የሽልማት ስነ ስርአት ከአስራ አንድ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ 27 ጋዜጠኞች በተለያዩ ዘርፎች እንደተሸለሙ ታውቋል፡፡
ጋዜጠኛው በእስር ላይ በመሆኑ ባለቤቱ ብርሃን ተስፋዬ እና ልጁ ፍትህ ውብሸት በስፍራው ተገኝተው ሽልማቱን ተቀብለዋል፡፡ ውብሸት በተወዳዳሪነት በቀረበበት ዘርፍ ከፍተኛ ፉክክር እንደነበር የሽልማቱ አዘጋጆች ገልፀው፤ ጋዜጠኛው በ“አውራምባ ታይምስ” ጋዜጣ ላይ በሚሰራበት ወቅት በፀረ - ሽብር ህጉ ተከሶ የ14 አመት እስራት እንደተፈረደበት አስታውሰው፤ ለነፃ ፕሬስ መጐልበት በከፈለው መስዋዕትነት ለሽልማት መመረጡን ጠቁመዋል፡፡

Read 2637 times