Saturday, 12 October 2013 12:06

የሪፖርተር ጋዜጣ አዘጋጅ አዋሳ ተወስዶ ታሰረ

Written by  ሰላም ገረመው
Rate this item
(3 votes)

በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ “በደቡብ ክልል ሶስት ምክትል ርዕሳነ መስተዳድሮች ከስልጣናቸው ተነሱ” በሚል ከወጣው ዘገባ ጋር ተያይዞ ከአዲስ አበባ ወደ አዋሳ ተወስዶ ለአንድ ቀን የታሰረው የሪፖርተር አዘጋጅ (ማኔጂንግ ኤዲተር) መላኩ ደምሴ፤ ትላንት ተለቆ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ፡፡
ከትላንት በስቲያ ሐሙስ ሶስት ሰዎች “በተጠረጠሩበት ወንጀል ይፈለጋሉ” የሚል መጥሪያ በመስጠት አዘጋጁን ከቢሮው እንደወሰዱትና እንደታሰረ የተገለፀ ሲሆን፤ ትላንት ጠዋት ፍ/ቤት ይቀርባል ተብሎ ቢጠበቅም “ዳኞች አልተሟሉም፤ ስንፈልግህ እንጠራሃለን” ተብሎ መለቀቁ ታውቋል፡፡

Read 4294 times