Print this page
Saturday, 05 October 2013 10:29

የሞዴስ መዘዝ

Written by 
Rate this item
(6 votes)

ሞዴስ ወንዶችንም ለሞት ሊያበቃ ለሚችል በሽታ ይዳርጋል

ሴቶች የወር አበባቸውን የሚያዩበት ዕድሜ በአኗኗር ሁኔታ፣ በአመጋገብና በአካባቢያዊ ሁኔታዎች ሊለያይ የሚችል ቢሆንም በአብዛኛው ከ14 ዓመት ዕድሜያቸው ጀምሮ የወር አበባቸውን ያያሉ፡፡
ምቾት ባለበት አኗኗር ውስጥ የሚያድጉ ልጆች፤ ከዚህ ዕድሜ ቀደም ብለው የወር አበባቸውን ሊያዩ ይችላሉ፡፡ ይህ ቀደም ባሉት ዓመታት የነበረው የወር አበባ ማያ የዕድሜ ገደብ ዛሬ ዛሬ እየወረደ መጥቶ ታዳጊ ሴት ህፃናቱ፣ በዘጠኝና በአስር ዓመት ዕድሜያቸው ላይ የወር አበባ ማየታቸው እየተለመደ መጥቷል፡፡ ህፃናቱ የሰውነታቸው ዕድገት ፈጣን እንደመሆኑ ሁሉ የውስጣዊ አካላቸው ዕድገትና ለውጥ እንዲሁ ፈጣን ነው፡፡ እነዚህ ታዳጊ ህፃናት የወር አበባ ምንነትና ሒደቱ በሰውነታቸው ላይ ስለሚያስከትለው ተፈጥሮአዊ ለውጥ ግንዛቤ ባላገኙበት ዕድሜያቸው ላይ ይህ ክስተት ሲገጥማቸው ለከፍተኛ ድንጋጤና የሥነልቡና ጫና መዳረጋቸው የማይቀር ነው፡፡
ችግሩ እንዳይከሰት ቤተሰብ በተለይም እናቶች ለሴት ታዳጊ ልጆቻቸው ስለወር አበባ ምንነትና የወር አበባ በሚመጣ ጊዜ ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች እንዲሁም በወር አበባ ወቅት የግል ንጽህናን በአግባቡ መጠበቅ እጅግ አስፈላጊነ መሆኑን በጊዜ ማስተማርና ልጆቻቸውን ማዘጋጀት እንደሚኖርባቸው የዘርፉ ባለሙያዎች ይናገራሉ። ልጆቹ ያላወቁትና ይከሰትብኛል ብለው ያላሰቡት ነገር ሲገጥማቸው ከፍተኛ ድንጋጤና የሥነልቡና ችግር እንደሚደርስባቸውም ባለሙያዎቹ ይገልፃሉ።
ቀደም ባሉት ዘመናት እናቶች የወር አበባቸው በሚመጣበት ጊዜ ከነጠላና አሮጌ ቀሚሶች ቅዳጅ እየቆረጡ በሚያዘጋጇቸው ጨርቆች የወር አበባቸውን እየተቀበሉ ንጽህናቸውን ይጠብቁ ነበር። ጨርቆቹ እየታጠቡ ከአንድ ጊዜ በላይ አገልግሎት እንዲሰጡ ይደረጉ ነበር፡፡ አሁንም ቢሆን በአገራችን በርካታ አካባቢዎች ጥቅም ላይ እየዋለ ነው። ሴቶች የወር አበባቸው በሚመጣበት ወቅት የሚጠቀሙበትና ንጽህናቸውን የሚጠብቁበት መንገድ በአብዛኛው ባህላዊና ተለምዶአዊ ነው፡፡
ዘመናዊነቱ እየተስፋፋ፣ ቴክኖሎጂው እያደገ ሲሄድ ለሴቶች የወር አበባ መቀበያነት የሚያገለግሉና የሴቶቹና ንጽህና የሚጠብቁ ሞዴሶች ተሰርተው ገበያ ላይ መዋል ጀመሩ፡፡ የእነዚህ ምርቶች ገበያ ላይ መዋል ሴቶች በወር አበባ ወቅት የሚሰማቸውን የህመም እና ያለመመቸት ስሜት በእጅጉ ከመቀነሱ ባሻገር፣ ንጽህናቸው በአግባቡ ባልተጠበቁ ጨርቆች ሳቢያ የሚከሰቱ ችግሮችን ለማስቀረት አስችሏል፡፡
በፋብሪካ ደረጃ እየተመረቱ በጥቅም ላይ የሚውሉ ዘመናዊ የወር አበባ መቀበያ ፓዶችም ሆኑ የወር አበባ መቀበያ እራፊ ጨርቆቹ እጅግ አደገኛ የሆኑ ችግሮችን እንደሚያስከትሉ ጥናቶች ጠቁመዋል፡፡ “ጆርናል ኦፍ ኢንፌክሽን ዲዚዝ” ይፋ ባደረገው መረጃ፤ በወር አበባ መቀበያ ሞዴሶች ሳቢያ የሚራቡት አደገኛ ባክቴሪያዎች ከሴቶችም አልፈው ወንዶችን ለህልፈተ ህይወት እየዳረጉ ነው፡፡ በወር አበባ ወቅት በሚፈሰው ደም ውስጥ ጉሉኮስን የመሰሉ ለባክቴሪያ መራባት እጅግ አስፈላጊና ምቹ የሆኑ ነገሮች ይገኛሉ፡፡ እነዚህም በወር አበባ መቀበያ ሞዴስ ውስጥ በመግባት በቀላሉ ለመራባትና ለመሰራጨት ይችላሉ፡፡
ስታፈሎከሰስ የተባሉት እጅግ አደገኛ ችግር ሊያስከትል ለሚችል በሽታ ምክንያት የሚሆኑት ባክቴሪያዎች “ቶክሲክ ሽክ ሲንድረም” የተባለና እስከ ሞት ሊያደርስ የሚችል አደገኛ የፍትወተ አካል ኢንፌክሽን ይፈጥራሉ፡፡ በአብዛኛው ችግሩ የሚከሰተው ረዘም ላለ ጊዜ ጥቅም ላይ በሚውሉ (በወር አበባ ወቅት በሴቷ ብልት ላይ ረዥም ሰዓት በሚቆዩ) ሞዴሶች ወይንም ንጽህናቸው በአግባቡ ባልተጠበቀና በተደጋጋሚ በጥቅም ላይ በሚውሉ የወር አበባ መቀበያ ጨርቆች አማካኝነት መሆኑንም መረጃ አመልክቷል፡፡ ችግሩን እጅግ የከፋ የሚያደርገው ሌላው ጉዳይ፤ ይህ በሞዴሱ ሳቢያ የሚከሰተው አደገኛ በሽታ ለወንዶችም መትረፉ ነው፡፡ የችግሩ ሰለባ ከሆነች ሴት ጋር የግብረ ስጋ ግንኙነት የፈፀሙ ወንዶችም “በቶክሲክ ሾክ ሲንድረም” መጠቃታቸው አይቀሬ ነው፡፡ ችግሩ በወቅቱ ታውቆ ተገቢው ህክምና ካልተደረገለትም ለሞት ሊያደርስ እንደሚችል መረጃው አመልክቷል።
የወር አበባ መቀበያ ሞዴሶች በሴቷ ሰውነት ላይ መቆየት የሚገባቸው ከ3-4 ሰዓታት መሆን ይገባዋል ያለው መረጃው፤ ከዚህ ለበለጠ ጊዜ የሚቆይ ከሆነ ለባክቴሪያ መራቢያ ምቹ ሁኔታዎች ስለሚፈጠሩ ይኸው ስታፍሎኮከስ ኦርስ የተባለው ባክቴሪያ ይራባና ”ቶክሲክ ሾክ ሲንድረም” የተባለውን አደገኛ በሽታ ሊያስከትል እንደሚችል ገልጿል፡፡
ይህ እጅግ አደገኛና በግብረሥጋ ግንኙነት ሳቢያ ከአንዱ ወደ አንዱ የሚተላለፍ በሽታ ከመከሰቱ በፊት ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባና ሴቶች በወር አበባ ወቅት የሚጠቀሙበትን ሞዴስ በንጽህና ሊጠቀሙበት እንደሚገባ “ጆርናል ኦፍ ኢንፌክሽን ዲዚዝ” አሳስቧል።

Read 8026 times
Administrator

Latest from Administrator