Saturday, 28 September 2013 13:25

ኢዮሃ

Written by  ገብረክርስቶስ ደስታ
Rate this item
(0 votes)

ኢዮሃ
አበባ ፈነዳ!
ፀሐይ ወጣ ጮራ
ዝናም ዘንቦ አባራ
ዛፍ አብቦ አፈራ፤
ክረምት መጣ ሄደ
ዘመን ተወለደ

አለም ሞቆ
ደምቆ
ብርሃን ሲያሸበርቅ
ጤዛው ሲብረቀረቅ
ህይወት ሲያንሰራራ
ፍጥረት ሲንጠራራ
ዘመን ተለወጠ መስከረም አበራ፡፡
“ኢዮሃ አበባዬ፡፡”
(1955)

Read 3120 times