በደራሲ አዳም ረታ ተፅፎ ለንባብ የበቃው “ግራጫ ቃጭሎች” የረጅም ልቦለድ መፅሐፍ ከስምንት አመታት በኋላ በድጋሚ ታትሞ በዚህ ሳምንት ለገበያ ቀረበ፡፡
ከደራሲው ተወዳጅ ስራዎች አንዱ የሆነው፣ ለአመታት ከገበያ ጠፍቶ የነበረውና ተፈላጊነቱ የጨመረው ይህ መፅሐፍ በ75 ብር እየተሸጠ ይገኛል፡፡
ደራሲው የተለየ የአፃፃፍ ስልትን እንዳሳየበት የሚነገረው “ግራጫ ቃጭሎች”፣ በኦላንድ አሳታሚዎች ታትሞ ነው ለገበያ የበቃው፡፡ ደራሲ አዳም ረታ በቅርቡም “የስንብት ቀለማት” የተሰኘ በአይነቱ ለየት ያለና ከአንድ ሺህ ገፆች በላይ ያሉት ረጅም ልቦለድ መፅሐፍ ለንባብ ያበቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡