Saturday, 28 September 2013 11:36

ቤተክህነት ሊወገዱ የነበሩ የብራና መጻሕፍት ተረከበ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን የቅርስ ጥበቃና የቤተመጻሕፍት ወመዘክርና ቱሪዝም መምርያ፤ በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ሊወገዱ የነበሩ ሦስት ጥንታዊ የብራና መጻሕፍትን ተረከበ፡፡ እንደ መምሪያው ገለፃ፤ ከቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ጊዜ ጀምሮ በቬርባል ሲገላበጡ ቆይተው ለመወገድ በዝግጅት ላይ የነበሩት የብራና መፃሕፍት የተገኙት በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አባል ጥቆማ ነው፡፡ መጻሕፍቱ በፖሊስ ኮሚሽን ግምጃ ቤት እንደሚገኙ በጠቆሙን መሰረት ተጻጽፈን ባለፈው ሰኞ መጻሕፍቱን ተረክበናል ብለዋል - የመምርያው ሃላፊ መምህር ሰለሞን ቶልቻ፡፡ የተገኙት የብራና መጽሐፍት እያንዳንዳቸው ከ200 ገጽ በላይ ሲሆኑ፤ መፃሕፍቶቹም ድርሳነ ኡራኤል፣ ድርሳነ ማህየዊ እና ድርሳነ ሚካኤል ናቸው፡፡ መምርያቸው ተመሳሳይ ሥራዎችን እየሰራ መሆኑን ሃላፊው ገልፀዋል፡፡

Read 2853 times