Print this page
Saturday, 28 September 2013 11:32

“…የFIGO አፍሪካ የመጀመሪያ ስብሰባ በኢትዮጵያ …”

Written by  ፀሐይ ተፈረደኝ (ከኢሶግ)
Rate this item
(0 votes)

እንደአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከኦክቶቨር 3-5/2013 ከመስከረም 22-24/2006 ዓ/ም FIGO የአለም የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ የጽንስና ማህጸን ሕክምና ፌደሬሽንን አህጉራዊ ስብሰባ በኢትዮጵያ ያካሂዳል፡፡ FIGO በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያን ጨምሮ 27/ሀገራት ያሉበት የአፍሪካ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር በሚል አህጉራዊ የስራ አካል እንደ ኤ/አ ኦክቶቨር 2012/ዓ/ም ያቋቋመ ሲሆን የዚህ አካል የመጀመሪያው ስብሰብ በ FIGO አስተባባሪነት እና በኢት ዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር አስተናጋጅነት ይካሄዳል፡፡ የስብሰባውን ሙሉ መንፈስ በመጪው እትም ለንባብ እናቀርባለን፡፡ በዚህ እትም የምናስነብባችሁ የቤተሰብ እቅድ ወይንም Family Planning ማለት ልጅን ካለመውለድ ጋር ብቻ የሚያያዝ ሳይሆን ፕሮግራሙ ልጅን ለመውለድ የሚደ ረገውን ክትትል እንደሚጨምርም የሚያሳይ ነው። “… አንድ ገጠመኝ ላካፍላችሁ፡፡ ...እኔ የምኖረው በአዲስ አበባ ነው፡፡ ባለቤ ደግሞ በስራ ምክንያት አብዛኛውን ጊዜውን የሚያሳልፈው በባህርዳር ነው፡፡ ባለቤ ቤተሰቡን ለመጠየቅ ወደ አዲስ አበባ የሚመጣው በአመት ሁለት ጊዜ ለዘመን መለወጫ እና ለት ንሳኤ በአል ብቻ ...ያውም ለአንድ ሳምንት ያህል ነው፡፡ በእንደዚህ ያለው አኑዋ ኑዋ ራችን...እኔ ሳረግዝ ...ስወልድ ልጆቻችን ስምንት ናቸው፡፡

እግዚሀር አልፈቀደለት ምና... ባለቤ ልጆቹን ሳያሳድግ ሞተ፡፡ እኔ በቤት ያሉት ልጆች ቁጥራቸው በዛ እያልኩ ስጨ ነቅ ...እሱ ለካንስ በሚሰራበት አካባቢ ሌላ ሴት አግብቶ ሶስት ልጆችን አፍርቶ አል፡፡ ለነገሩ...ንብረት የለንም...የምንጨቃጨቅበት ምንም ነገር አልገጠመንም፡፡ ይሁን እንጂ እኔም ሆንኩ ጉዋደኛው የቤተሰብ እቅድ ዘዴን ሳንጠቀም ልጆችን በመውለዳችን ለማሳ ደግ ተቸግረናል ... ከላይ ያነበባችሁት ገጠመኝ አስተያየት ሰጪዋ እንዳሉትም የቤተሰብ እቅድ ዘዴን አለመጠቀም በብዙዎች ዘንድ ውጤቱ ምን ያህል አስቸጋሪ እንደሚሆን ነው፡፡ በዚህ ዙሪያ ዶ/ር ዮናስ ጌታቸው የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት ማብራሪያ ሰጥተውናል፡፡ ጥ/ የቤተሰብ እቅድ Family Planning ሲባል ምን ማለት ነው? መ/ Family Planning ¨ይንም የቤተሰብ እቅድ ማለት ሴቶችና ወንዶች በፈለጉት ጊዜ የፈ ለጉትን ያህል ልጅ መውለድ እንዲችሉ የሚያቅዱበት ዘዴ ነው።

በዚህም ምን ያህል ልጅ በምን ያህል የጊዜ ልዩነት መውለድ እንደሚፈልጉ አስቀድሞውኑ በመወሰን የሚ ወለዱት ልጆች በቂ በሆነ አቅም ...ማለትም አቅም በፈቀደ መጠን የትምህርት የህክምና እንዲሁም የተመጣጠነ ኑሮ እንዲያገኙ የሚያስችላቸው አሰራር ነው፡፡ በእርግጥ የቤተ ሰብ እቅድ ሲባል ሴቶችና ወንዶች መውለድ ባልፈለጉበት ጊዜ እንዳይወልዱ ማድረግ ብቻ ሳይሆን መውለድ ካልቻሉ እንዲወልዱ ለማድረግም የሚጠቀሙበት ዘዴ ነው፡፡ ጥ/ ልጅ መውለድ ለሚፈልጉ የቤተሰብ እቅድ (Family Planning) እንዴት ያገለግላል? መ/ ከላይ እንደተገለጸው የቤተሰብ እቅድ ሲባል ልጅ መውለድ ለማይፈልጉ የእርግዝና መከ ላከያን በመጠቀም የልጅ ቁጥርንና ጊዜን ለመወሰን የመርዳቱን ያህል በዚህ ፕሮግ ራም ልጅ መውለድ ያልቻሉም መውለድ እንዲችሉ የሚያስችል አሰራር አለው፡፡ ሴቶ ችና ወንዶች ልጅ መውለድ ባልቻሉበት ወቅት ወደሐኪም በመቅረብ ባልና ሚስቱ መውለድ ያልቻሉባቸው ምክንያቶች በሕክምና በምርመራ ታውቆ ወደቀጣይ እርምጃ እንዲሄዱ ያስችላል፡፡

ጥ/ ልጅ መውለድ ለሚፈልጉ በFamily Planning ምን አይነት ሕክምና ይሰጣል? መ/ ልጅ መውለድ አለመቻል ሲባል ምናልባት በሴቷ ወይንም በወንዱ ምክንያት የተከሰተ ሊሆን ይችላል። ለምሳሌ በሴቷ በኩል ከሆነ ምክንያቶቹ፡- የተፈጥሮ ችግር እና የሆርሞን መዛባት፣ የዘር ፍሬ አለመኖር፣ የማህጸን በር ተስተንክሎ አለመፈጠር፣ የወንዱ ፈሳሽ በትክክል ከእንቁላል ጋር እንዳይገናኝ ምክንያት ይሆናል፡፡ የሴቷ እንቁላልና የወንዱ እስፐርም የሚገናኙበት (fallopian tube) የሚባለው መስርመር በተለያዩ ምክንያቶች መዘጋት፣ በዚህ መስመር ላይ የሚከሰት የተለያየ ቁስለት መመረዝ ወይንም ጠባሳ የሴቷ እንቁላል ከወንዱ ስፐርም ጋር እንዳይገናኝ ያውካል፡፡ ለሴቶች ልጅ ያለማግኘት ምክንያት ከሚሆኑት መካከል የሆርሞን መዛባት ይገኝበታል፡፡ሴቶች የወር አበባቸው ጊዜ ከመድረሱ በፊት ወደአጋማሽ በሚሆነው ቀን አንድ እንቁላል ለእርግዝና ዝግጁ የምትሆን ሲሆን ይህ እንቁላል በጊዜው እስፐርም ካላገኘ እርግዝና መሆኑ ቀርቶ በወር አበባ መልክ ይፈሳል፡፡ ይህ ለሴቶች ልጅ ያለመውለድ 25% ድርሻ ይይዛል፡፡

በወንዶች በኩል ልጅ ያለመውለድ ችግር፡- የአባላዘር በሽታ እንደ ጎኖሪያ...ጨብጥ...ወዘተ የዘር ፍሬ አለመኖር፣ የዘር ማስተላለፊያ ቱቦው በተለያየ ምክንያት ሲዘጋ፣ የወንድ የዘር ፍሬ እንቁላልን የመስበር አቅም ከሌለው፣ የእስፐርም መጠን ማነስና እንቅስቃሴው አዝጋሚ መሆን፣ የእስፐርም ጥራት መጉዋደል፣ በተለያዩ ምክንያቶች በብልት አካባቢ ጉዳት ደርሶበት ከነበረና ያም በጊዜው ሳታከም ቀርቶ ወደመመረዝ ወይንም ወደህመም ከተለወጠ ...ወዘተ፡፡ አንዳንድ ጊዜም ሴቶችና ወንዶች ያለመጣጣም ችግር ሊኖራቸው ይችላል፡፡ ከላይ በተጠቀሱትና በሌሎችም ምክንያቶች ልጅ መውለድ ያልቻሉ ሴቶችና ወንዶች በቤተሰብ እቅድ አገልግሎት Family Planning ፕሮግራም መሰረት ወደሕክምና ባለሙያ ቀርበው አስፈላጊውን ሕክምና ቢያደርጉ ልጅ መውለድ የሚችሉበትን አጋጣሚ መፍጠር ይቻላል፡፡ ጥ/ ያለመጣጣም ሲባል ምን ማለት ነው? መ/ ያለመጣጣም ሲባል በተለያየ መንገድ የሚታይ ሲሆን በተለይም የወንድ የዘር ፍሬና የሴት የዘር ፍሬ ቢገናኙም ዘር ለመፍጠር ካልቻሉ እንዳልተጣጣሙ ይቆጠራል፡፡

ይህ አጋጣሚ በተለያየ ምክንያት ሊፈጠር የሚችል ነው፡፡ ለምሳሌም ...እንደ ጎኖሪያ ወይንም ጨብጥ የመሳሰሉት በሽታዎች ምክንያት ከሚፈጠሩት ሕመሞች መነሻነት የሚፈጠረው ኢንፌክሽን ከወንድየው ለሚወጣው ፈሳሽ ችግር ሊፈጥር ይችላል፡፡ በሌላም በኩል በማ ህጸን በር አካባቢ ያለው (mucus) ማለትም ማህጸንንና የማህጸን በርን ከተለያየ መመረዝ የሚከላከ ለው ወፈር ያለ ፈሳሽ ምናልባትም ለወንዱ ፈሳሽ የሚወፍርበት ከሆነና ፈሳሹ ያንን ማለፍ ካቃተው ወይንም ለወንዱ ፈሳሽ መርዝ የሚሆን ከሆነ እንደ አንድ አለመጣጣም ሊቆጠር ይችላል፡፡ ስለዚህ ከላይ በተገለጹትና ሌሎችም ተመሳሳይ ምክንያቶች ልጅን ማፍራት ያልቻሉ ሰዎች የስነተዋልዶ አካሎቻቸውን በተገቢው በመፈተሸ የህክምና ምርመራ ማድረግ እና ሴቶችም ሆኑ ወንዶች የሚሰጣቸውን መድሀኒትም ሆነ ሌላ የህክምና አገልግሎት በተገቢው መከታተል ይጠበቅባቸዋል፡፡ የወንዶች እስፐርም ጥራትና ብዛት ወይንም የሴቶችን ማህጸን አፈጣጠርና እንቁላል ማምረት አለማምረት የመሳሰሉት በተገቢው የህክምና ድጋፍ ካገኙ የነበሩበት ሁኔታ ሊሻሻል ይችላል፡፡ አንዳንድ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በተለይም በሆርሞን መዛባት የሚከሰቱ ልጅ የመውለድ ችግሮች እስከ 75 ኀ ያህል በህክምና ፈውስን ያገኛሉ፡፡

ጥ/ አስፈላጊ የሆነው ሕክምና ሁሉ በኢትዮጵ ሊሰጥ ይችላልን? መ/ በእርግጥ ልጅ መውለድ ለተቸገሩት ለሁሉም አይነት ምክንያቶች ሕክምናውን በኢትዮጵያ መስጠት ይቻላል ማለት አይቻልም፡፡ ነገር ግን በአገር ውስጥ የሚሰጡትን ሕክምናዎች በአግባቡ በመጠቀም ብዙዎች ውጤታም እንደሆኑ መመስከር ግን ይቻላል፡፡ ልዩነቱ በተለይም በሴትዋም ይሁን በወንዱ በኩል የሚፈጠሩትን የመውለድ ችግሮች እስከመጨረሻው ሕክምናው ተሞክሮ ነገር ግን ውጤታማ አልሆን ሲል በሳይንሳዊ ዘዴ በማዳቀል ልጅ እንዲያገኙ ለማድረግ በኢትዮጵም ሆነ ሌሎች ተመሳሳይ ሀገራት መሳሪያው ስለሌለ ብዙዎች ሕክምናው ወደሚሰጥበት ሀገር በመሄድ ልጅ ማግኘት ይሞክራሉ። ስለዚህ ሕክምናው ይሰጣል አይሰጥም ለሚለው በዚህ ሀገር ባለው የህክምና አሰጣጥ ደረጃ ታክመው መፍትሔ የሚያገኙ የመኖራቸውን ያህል ወደውጭም ሄደው መፍትሔ የሚያገኙ አሉ፡፡ ጥ/ የእርግዝና መከላከያ ኪኒን እርግዝና እንዲፈጠር ሊያደርግ ይችላልን? መ/ የእርግዝና መከላከያ ኪኒን የእርግዝና መከላከያ እንጂ ለመውለድ የሚረዳ አይደለም፡፡ ነገር ግን ሴቶች የወር አበባ መዛባት ሲያጋጥማቸው ለተወሰኑ ጊዜያት እንዲወስዱት ይመከራል፡፡ የዚህም ምክንያቱ የወር አበባ መዛባት ባለበት ሁኔታ እርግዝናን ማሰብ ስለማይቻል ነው። ስለዚህ የወር አበባቸው እንዲስተካከል በሚደረገው ሕክምና ለሶስት ወር ያህል የእርግዝና መከላከያ ኪኒን እንዲወስዱ ይደረግና ከዚያ በሁዋላ እንዲያረግዙ ይደረጋል።

Read 5726 times