Saturday, 28 September 2013 11:00

ዶ/ር ነጋሶ ለ3 ሰዓት ታስረው ተፈቱ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፤ ባለፈው ረቡዕ ለሦስት ሰዓታት በፖሊስ ጣቢያ ታስረው መፈታታቸው ተገለፀ፡፡ ዶ/ር ነጋሶ፤ ፓርቲው ነገ ያካሂዳል ተብሎ ለሚጠበቀው ሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ እንዲያደርጉ ካሰማራቸው አባላት ጋር በተያያዘ ታስረው እንደነበር ታውቋል፡፡ ባለፈው ረቡዕ የሰላማዊ ሰልፍ ቅስቅሳ ሲያደርጉ የነበሩ 14 የፓርቲው አባላት “የቅስቀሳ ፈቃድ የላችሁም” ተብለው በፖሊስ መያዛቸውን የገለፀው ፓርቲው፤ የአንድነት ልሳን ጋዜጣ ፎቶግራፍ አንሺም በራሪ ወረቀት ሲቀበሉ የነበሩ ሰዎችን ያለፍላጐታቸው ፎቶግራፍ አንስቷል፤ ተሳድቧል በሚል ክስ እንደቀረበበት አስታውቋል፡፡ ዶ/ር ነጋሶ የሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ እንዲደረግ ለአባላቱ የስምሪት ደብዳቤ በመፈረማቸው፣ ድርጊቱ የተፈፀመው እሳቸው በሰጡት አመራር እንደሆነ በፖሊስ ተገልፆላቸው ጉዳዩ እስኪጣራ መታሰራቸውን ነው ፓርቲው የገለፀው፡፡ ከሶስት ሰዓት እስር በኋላም ፎቶግራፈሩ በዋስ ሲለቀቅ ዶ/ር ነጋሶ በነፃ እንደተለቀቁ ታውቋል፡፡

Read 7737 times