Saturday, 21 September 2013 11:32

የጥላሁን ገሰሰ መታሰቢያ አርብ ይቀርባል በቴአትር ጥበብ የሠለጠኑ ዛሬ ይመረቃሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የክብር ዶ/ር ጥላሁን ገሰሰ መታሰቢያ ዝግጅት በመጪው አርብ ከቀኑ 8 ሰዓት እንደሚቀርብ የኢትዮጽያ ብሔራዊ ትያትር አስታወቀ፡፡ በትያትር ቤቱ በሚቀርበው የሙዚቃ ዝግጅት፣ ከኢትዮጵያውያን አርቲስቶች በተጨማሪ ከሱዳን የመጣ የሙዚቃ ቡድን ጣዕመ ዜማዎችን በነፃ ለታዳሚዎች ያቀርባሉ፡፡ ዝግጅቱ የሚቀርብበት ዕለት ዐርብ መስከረም 17 የከያኒው የልደት ቀን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በሌላም በኩል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር ባለፈው ዓመት ክረምት “በመሠረታዊ የቴአትር ጥበብ” ዘርፍ ያሠለጠናቸውን ተማሪዎች ዛሬ ከጧቱ 3 ሰአት እንደሚያስመርቅ አስታወቀ። 60 ለሚሆኑ ተመራቂዎች ሥልጠናውን በትያትር ዝግጅት ጌትነት እንየው፣ በጽሑፈ-ተውኔት ተስፋዬ ገብረማርያም እንዲሁም በትወና ሳሙኤል ተስፋዬና መሠረት ሕይወት ሥልጠናውን እንደሠጡ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 1844 times