Print this page
Monday, 16 September 2013 08:14

“48ቱ የአሸናፊነት ሚስጥራት” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(80 votes)

“The 48 Laws of power” የተሰኘው የሮበርት ግሪን መፅሃፍ “48ቱ የአሸናፊነት ሚስጥራት” በሚል በእስክንድር ስዩም ተተርጉሞ ለንባብ በቅቷል፡፡
በ48 ምስጢሮች የተከፋፈለው መፅሃፉ፤ “ከአለቃይ በልጠህ ለመታየት አትሞክር”፣ “በሌሎች ዘንድ ተፈላጊ መሆንን እወቅበት”፣ “ፍላጐትህን ላገኘኸው ሁሉ በግልፅ አትናገር”፣ “ሁሌም ከደሙ ንፁህ ለመሆን ጥረት አድርግ” የሚሉና ሌሎች ርዕሶችን ይዟል፡፡ በ161 ገፆች ተቀንብቦ የተዘጋጀው መፅሃፍ፤ በታዋቂ ሰዎች አባባልና ጥቅሶች የታጀበ ሲሆን በ39 ብር ከ45 ለገበያ ቀርቧል፡፡ ተርጓሚው ከዚህ ቀደም “ስኬታማ የጊዜ አጠቃቀም”፣ “የፍቅር መፍትሄ” እና “ወርቃማ የፍቅር ጥቅሶችና አባባሎች” የተሰኙ መፅሃፍትን ለንባብ ማብቃቱ ይታወቃል፡፡

Read 22340 times
Administrator

Latest from Administrator