የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የትያትር ትምሕርት ክፍል ለመክፈት በቅድመ ዝግጅት ላይ መሆኑ ታወቀ፡፡ ለዚሁ ቅድመ ዝግጅት ይረዳ ዘንድ የዩኒቨርሲቲው የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ትምሕርት ክፍል ምሁራን እና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው ኃላፊዎች፤ የሀገሪቱን ከፍተኛ የትምሕርት ተቋማት እየጎበኙ ነው፡፡ የአዲስ አድማስ ምንጮች የትምሕርት ክፍሉ በ2006 ዓ.ም የትምሕርት ዘመን እንደሚከፈት የገለፁ ሲሆን በዩኒቨርሲቲው የኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነጽሑፍ አማርኛ ትምሕርት ክፍል ኃላፊ አቶ አማረ ተሾመ ግን “አንድ ባልደረባችን ባቀረቡት ፕሮፖዛል መሠረት የቅድመ መነሻ ሀሳብ ለማቅረብ በዝግጅት ላይ ነን፡፡ በትክክል መቼ እንደምንከፍት አልወሠንንም” ብለዋል፡፡