Saturday, 07 September 2013 11:49

የግጥም በጃዝ 26ኛ ዝግጅት ለእንቁጣጣች ይቀርባል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በራስ ሆቴል ትልቁ አዳራሽ እየቀረበ ያለው “ግጥም በጃዝ” 26ኛ ዝግጅቱን በመጪው ረቡዕ መስከረም ፩ እንደሚያቀርብ አዘጋጆቹ አስታወቁ። በረቡዕ ልዩ ዝግጅት አበባው መላኩ፣ ግሩም ዘነበ፣ ደምሰው መርሻ፣ ነቢይ መኮንን የግጥም ሥራዎቻቸውን ፋቡላ የኪነጥበባት ማሕበር “ከነፃ አውጪ” ባንድ ጋር በመሆን የሥነ ቃል ትርዒት ያቀርባሉ፡፡ ከቀኑ 11 ሰዓት ጀምሮ በሚቀርበው ዝግጅት የፍልስፍና ምሁሩ ዶር. ዳኛቸው አሰፋ ዲስኩር ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Read 1362 times