Saturday, 07 September 2013 11:48

ኤልቤት ነገ የዐውደዓመት ዝግጅት ያቀርባል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ፒያሳ አካባቢ የሚገኘውና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዓላትን ከነትውፊታዊ ይዘታቸው በማክበር የሚታወቀው ኤልቤት ሆቴል የ2006 ዓ.ም መጀመርያ ዐውደዓመትን ዋዜማ በባሕላዊ ይዘት እንደሚያከብር አስታወቀ፡፡ ከቀኑ 11 ሰዓት በመጀመር በሚቀርበው ዝግጅት ወጣቶች የባህል ልብስ ለብሰው “አበባየሆሽ” ብለው የሚዘፍኑበት ሲሆን የዘመን አቆጣጠርን አስመልክቶ ማብራሪያ በባለሙያ ይሰጣል፡፡ በዝግጅቱ የባሕል ዘፈኖች፣ ግጥሞችና መጣጥፍ እንደሚቀርቡና የችቦ ማብራት ሥነ ሥርአትም እንደሚኖር ይጠበቃል።

Read 1517 times