Print this page
Saturday, 07 September 2013 10:02

የኢ/ር ኃይሉ ሻውል መፅሀፍ ሰኞ ይወጣል

Written by 
Rate this item
(5 votes)

በቅርቡ ከመኢአድ ሊቀመንበርነታቸው በመልቀቅ በፓርቲው የበላይ ጠባቂነት የቀጠሉት የኢ/ር ኃይሉ ሻውልን የህይወት ታሪክ የያዘ መፅሀፍ ከነገ በስቲያ ለንባብ እንደሚበቃ የመፅሀፉ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ፍሬው አበበ ገለፀ፡፡ “ህይወቴና የፖለቲካ እርምጃዬ” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው መፅሃፉ፤ የኢ/ር ኃይሉ የህይወት ውጣ ውረድና የፖለቲካ ተሳትፎ ላይ እንደሚያተኩር አዘጋጁ ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡
በተለይም ከ97 ምርጫ ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ክስተቶችና ለቅንጅት መፍረስ ምክንያት ነው ያሉትን ጉዳዮች ያሳዩበት መፅሃፍ እንደሆነ የገለፀው አዘጋጁ፤ ከምርጫው ጋር ተያይዞ የቅንጅት አመራሮች መታሰር፣በእርቅ መንፈስ የተጀመረው ሽምግልና እንዴት ወደ ይቅርታ መጠየቅ እንደተቀየረ፣ በእስር ላይ የነበረው የቅንጅት አመራር ክፍፍል ምን መልክ እንደነበረው እና መሰል ጉዳዮችን የሚተነትኑ አዳዲስ መረጃዎች እንደተካተቱበት አብራርቷል፡፡
“በተለይ ኢንጂነር ኃይሉ ሻውል የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ ችግሮች ሁሉ ወደ ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ብቻ ሳይወረውሩ፣ በራሱ በተቃውሞ ጎራው ያሉትንም ችግሮች አንድ በአንድ ነቅሰው በመፅሀፋቸው ለማሳየት መቻላቸው፣ ለአገሪቱ ፖለቲካዊ ችግሮች መፍትሄ ለሚሹ ወገኖች ሁሉ ጥሩ መረጃ የሚሰጥ እንደሚሆን ይታመናል” ብሏል አዘጋጁ፡፡ የመፅሃፉ ሁለተኛ ክፍል በአዲሱ ዓመት ለንባብ እንደሚበቃም ለማወቅ ተችሏል፡፡ የፊታችን ሰኞ በ55 ብር ለገበያ የሚቀርበው የኢንጅነሩ መፅሃፍ፤ በስድስት ክፍሎችና በ175 ገፆች ተቀንብቦ የተዘጋጀ ነው ተብሏል፡፡

Read 17911 times
Administrator

Latest from Administrator