በኢንጂል አይስ ፊልም ፕሮዳክሽን የተዘጋጀውና በደራሲ ዮናታን ወርቁ የተደረሰው ላ-ቦረና ፊልም፣ የፊታችን ሰኞ በ11 ሰዓት በብሄራዊ ትያትር ቤት ይመረቃል፡፡ በላይ ጌታነህ ዳሬክት ያደረገው ፊልሙ፣ በአንዲት ፈረንሳዊት አንትሮፖሎጂስት ጥናት ላይ ያተኮረ ሲሆን የቦረናን ባህልና ወግ ያንፀባርቃል ተብሏል፡፡ በፊልሙ ላይ አለም ሰገድ ተስፋዬ፣ ማርያኔ ቤለርሰን፣ አንተነህ ተስፋዬና ሌሎችም ተውነውበታል፡፡ ፊልሙ የ1፡40 ርዝማኔ እንዳለውም ተገልጿል፡፡