አቢሲኒያ ባንክ ዘንድሮ 351.2 ሚሊዮን ብር አጠቃላይ ትርፍ ማግኘቱንና ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ12.2 በመቶ ብልጫ እንዳለው ገለፀ፡፡ ባንኩ በላከው መግለጫ ላይ እንዳስታወቀው፤ የባንኩ አጠቃላይ ገቢ 895 ሚሊዮን ብር መድረሱንና ካለፈው ዓመት በ126 ሚሊዮን ብር ብልጫ ያለው መሆኑን ጠቁሟል፡፡ ለተለያዩ የንግድና አገልግሎት ዘርፎች በአጠቃላይ 4.7 ቢሊዮን ብር ብድር የሰጠ መሆኑን የገለፀው ባንኩ፤ አጠቃላይ ተቀማጭ ሂሣቡ 8.5 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቋል፡፡ አቢሲኒያ ባንክ 371ሺ 420 የሚሆኑ የገንዘብ አስቀማጭ ደንበኞች እንዳሉት መግለጫው ጠቅሶ፤ በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞችና ክልሎች 82 የሚደርሱ ቅርንጫፎችን ከፍቶ ለደንበኞቹ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ አመልክቷል፡፡
Published in
ዜና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል