Saturday, 31 August 2013 11:44

ደ.ኮርያ ለስልጠና ተልከው የቀሩት ኢትዮጵያውያን የተቃውሞ ሰልፍ ሊያደርጉ ነው

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(4 votes)

ለስልጠና ወደ ደቡብ ኮርያ ተልከው እዚያው ጥገኝነት ጠይቀው የቀሩት 39 ኢትዮጵያውያን፤ የኢትዮጵያን መንግሥት በመቃወም የፊታችን ረቡዕ በደቡብ ኮርያ ዋና ከተማ ሴኡል የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚያደርጉ አስታወቁ፡፡
በአውቶ መካኒክ፣ በዌልዲንግና በኤሌክትሪሲቲ ሰልጥነው ተመልሰው ሀገራቸውን እንዲያገለግሉ መንግሥት የላካቸው እነዚህ ወጣቶች፤ በችግር ላይ እንደሆኑ ተደርጐ የተነገረው ሐሰት መሆኑን ጠቅሰው፤ ሰብአዊ ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆላቸው በሴኡል እየኖሩ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ወጣቶቹ የፊታችን ረቡዕ “በኢትዮጵያ ያለው የሰብአዊ መብት ጥሰት ይቁም”፣ “የሙስሊም ወንድሞቻችን ችግር እኛንም ይመለከተናል”፣ “መንግሥት ከሃይማኖት ጉዳዮች ላይ እጁን ያንሳ” የሚሉ ጉዳዮችን በማንሳት በሴኡል ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያካሂዱ ከስፍራው በስልክ ገልፀዋል፡፡

Read 15815 times