ታላቁ የፖፕ ሙዚቃ ንጉስ ማይክል ጃክሰን ከሞተ አራት አመት ሆነው፡፡ የሟቹ ቤተሰብ ግን አሁንም የሞቱ ምክያኒያት አልተዋጠልኝምና ይመርመርልኝ ማለቱን ቀጥሏል፡፡ ምርመራው በአንደኛነት ያነጣጠረው የሙዚቃ ንጉሱን የልብ ጤና ይከታተል በነበረው ዶክተር ኮንራድ ሙሬ ላይ ነው፡፡ የክሱ አይነት፡- በስህተት ነብስ ማጥፋት (involuntary manslaughter) እና የታማሚውን የጤና ሁኔታ ያላገናዘበ ንዝህላልነት የሚል ነው፡፡ በዚህ ፍርድ ሂደት ላይ የማይክል ጃከሰን የቀድሞ ሚስት (ዴቢ ሮው) በእንባ እየታጠበች ስለ ሟቹ ባሏ ባህሪ ተናዝዛለች፡፡ ትዝታዋን በመመርኮዝ የሰጠችው ምስክርነት የዚህ ሳምንት ትኩስ ዜና ሆኖ ሰንብቷል፡፡