ስምንተኛው የበደሌ ስፔሻል “የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ፊልም ፌስቲቫል በህዳር 2006 ዓ.ም እንደሚካሄድ ሊንኬጅ ማስታወቂያ ህትመትና ፕሮሞሽን አስታወቀ፡፡ ከህዳር 16 እስከ ህዳር 23 የሚካሄደው ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫል፣ “አፍሪካዊያን የራሳቸውን ታሪክ እስኪናገሩ የቅኝ አገዛዝ ታሪክ ቅኝ ገዢዎችን ያደምቃል” በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ ሲሆን 70 ያህል ዶክመንተሪ፣አጭር፣ፊቸር እና አኒሜሽን ፊልሞች ይቀርቡበታል፡፡ “African panorama” “Cinema Landmarks” “Contemporary Cnema”, “Regional /Ethiopia Focus” እና “Community Focus” የተሰኙ ፊልሞች የሚቀርቡበት ፌስቲቫል፣ ሽልማቶችም ይኖሩታል ተብሏል፡፡